ሳይንስ, ባህል, ታሪክ, Uncategorized

እንሰት – ከቆጮና ቡላ ባሻገር

ይህ ጽሁፍ የእንሰትን ዘርፈብዙ ጠቀሜታና ታሪክ በተለይም መድኃኒትነቱ ላይ  ያተኮረ ይሆናል። እንሰት፤ በሳይንሳዊ ስሙ እንሰት ቬንትሪኮሰም (Enset ventricosum or edule) ከዓለም ሁሉ በኢትዮጵያ ብቻ በምግብነት ጥቅም ላይ የዋለ ዘረ ሙላዱም ከኢትዮጵያ የሆነ የተክል ዓይነት ነው። የአገሪቷ አንድ አምስተኛ (20%) የሚሆነው ሃያ ስድስት ሚሊዮን (26 ሚሊዮን) ሕዝብ የእንሰት ተጠቃሚ እንደሆነ ይገመታል። ተክሉና ዝርያው ከሙዝ ጋር ተመሳሳይ ስለሆነ በእንግሊዝኛ “የውሽት ሙዝ” (false banana) ተብሎ ይታወቃል። እንሰት ከሶስት መቶ በላይ የተለያዩ ዝርያዎች አሉት። ግንዱ፤ ስሩ፤ ቅጠሉ (ኮባው) እና ቃጫው በብዛት ጥቅም ላይ ይውላሉ። እንሰት ከአስር ሺህ ዓመታት በላይ በኢትዮጵያ ሰሜን፥ ደቡብና ምዕራብ የታወቀና ጥቅም ላይ የዋለ እንደሆነ ታሪክ ይናገራል።  በጣና ሐይቅ፣ በሰሜን ተራሮች ዙሪያ እንዲሁም እስከ ሰሜን አዲግራትና በደቡብ ኤርትራ በማእከላዊና ሰሜን ደጋማ አካባቢዎችም ያድግ እንደነበር ታሪክ ያስታውሳል። እንሰት ከሶስት መቶ በላይ የተለያዩ ዝርያዎች አሉት። እንደ ዝርያዎቹ ዓይነት ጠቀሜታዎቻቸውም እንዲሁ ይለያያሉ፤ ለምሳሌም ድርቅንና በሽታን ለመከላከል፤ ለመድኃኒነት፤ ለምግብነት፤ ለቤት መገልገያ፤ ለኢንዱስትሪ ግብአትነት ወዘተ። እንሰት በጉራጌ እሴት/እሰት፥ በሲዳሞ ዊሴ፥ በዳውሮና ወላይታ ኡጦ፥ በጌዴዎ ዎርኪቻ፥ በሃዲያ ስልጤና ከምባታ ዊሳ፥ በትግሬ ጉና ጉና በመባል ይታወቃል። ለብዙ የቤት አገልግሎት የሚውለው ቅጠሉ ኮባ ይባላል።  በምግብነት የሚቀርበው ደግሞ እንደ አካባቢው ቆጮ (ዉሳ፥ ዋሳ፥ ወርቄ…)፥ አሚቾ፥ቡላ ወዘተ እየተባለ ይጠራል።
የእንሰትን ጠቃሚነት እንደሌሎች አዝእርቶች  እውቅና መስጠት፤ የወደፊቱ አንዱ የግብርና ምሰሶ ማድረግ፤ በዋጋ ዝቅተኝነትና አትራፊ የሆኑ ምርቶች ላይ በማትኮር የእንሰት ግብርና እንዳይመነምን የእንሰት አምራቾች እንዲበረታቱ ማድረግ ይገባል።
(ሙሉ ጽሑፉን ለማንበብ ዓርእስቱን ይጫኑ)

ሥነጽሑፍ

መጽሐፈ ምሳሌ ዘጨዋ ተረት፤ እውሩና አንካሳው

ባንድ ከተማ ሽፍታ መጥቶ  ሰው ሁሉ ነፍሱን ለማዳን ሸሸ። ሁለት ሰዎች ቀሩ ይላሉ። እነርሱም እውርና አንካሳ ናቸው። እውሩም የሚመራው ፣ አንካሳውም የሚሸከመው አጥተው ተጨነቁ። ስለዚህ ተማከሩ። እውሩ አንካሳውን ተሸከመው፤ በእውሩ እግር በመፃጉዑ ዓይን እንደ አንድ ሰው ሆነው ሀገር ወዳለበት ደረሱና ነፍሳቸውን ከሞት አዳኑ። ሰው ሁሉ እንዲሁ በምክር ቢተባበር ደኅንነት ይሆንለታል።

ሥነጽሑፍ, ባህል

ስለ ባህል አንዳንድ ነጥቦች – የመነሻ ሀሳብ

ኢትዮጵያ የብዝሀ ብሄረሰቦችና ማህበረሰቦች ሀገር ናት፡፡ እነዚህ የኢትዮጵያ ብሄረሰቦችና ማህበረሰቦች አንደየአካባቢያቸው የተፈጥሮና የአየር ንብረት አንዲሁም በአንድ በኩል በተናጠል በሌላ በኩል ደግሞ እርስ በርስ ባደረጓቸው መስተጋብሮች የፈጠሯቸው ብዝሀ ባህላዊ እሴቶች አሏቸው፡፡ እነዚህ ብዝሀ ባህላዊ እሴቶች ለፈጠሯቸው የህብረተሰብ ክፍሎች እየሰጡት ካሉ ፖለቲካዊ ፣ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጠቀሜታዎች በዘለለ በአገር አቀፍ ደረጃ አንድ የፖለቲካ እንዲሁም ተደጋጋፊ የኢኮኖሚ ማህበረሰብ በመፍጠሩና ጠንካራ ሀገረ መንግስት በመገንባቱ ረገድ የበኩላቸውን የማይታለፍ ድርሻ እንደሚወጡ ይታመናል፡፡ በዚህ የባህል አምድ ስር ስለ ባህል በአጠቃላይ፤ የባህል ምንነት ጠቀሜታና አተገባበር ከኢትዮጵያ አጠቃላይ ብሄረሰቦችና ማህበረሰቦች እንዲሁም አለም አቀፍ ተሞክሮ አንጻር ሃሳቦችን እየሰደርን የምናቀርብ ይሆናል፡፡ ጽሁፉ ተከታታይነት ባለው መልክ የሚቀርብና ሁሎቹንም የባህል ዘውጎችና ዘርፎች የሚዳስስ ሲሆን፤ ለዛሬ የባህልን ትርጓሜ፤ አለም አቀፍና አገር አቀፍ አተያይ በማሳያነት በማቅረብ አሃዱ ብለናል።

ሥነጽሑፍ, ባህል

ሌስላውን ዘረፋ – አጭር የምርምር ማስታወሻ

ይህ አጭር ማስታወሻ የሴማዊ ቋንቋዎች ጥናት አባት ተብለው የሚታወቁት ዎልፍ ሌስላው (Wolf Leslau) በ1961 የዐማርኛ የገደል ማሚቶ ጥምር ቃላት የተሰኘውን መጣጥፋቸውን ለመቃኘትና እውቅና ለመስጠት በአቶ ዳናኤል አበራ ተዘጋጅቶ ቀርቦአል። ሌስላው በጥናቱ ላይ 80 ጥምር ቃላቶችን በመለየት በማሳያነትም እንደ አርቲ ቡርቲ …እንቶ ፈንቶ የሚሉትንና “ምንም ቁም ነገር የለውም… የማይረባ ነው…” ለማለት የሚጠቅሙትን ገልጸዋል። በአሁኑ ጊዜ ከእነዚህ 80 ጥምር ቃላት መካከል 25ቱ ጥቅም ላይ የዋሉ ሲሆኑ 11 ቃላትን አቅራቢው ጨምረዋል ። እነዚህ አስተጋቢ ቃላቶች ከ6 ሚሊዮን የአማርኛ ቃላት ጋር ተጣጥመው ተገኝተዋል።

የሕይወት ታሪክ, ጥናትና ምርምር, ፖለቲካ

የታኅሳስ 1953 ዓ.ም ግርግር በከፊል – ከሻለቃ ያሬድ ቢተው – ዋሺንግተን ዲሲ፣ ሰሜን አሜሪካ – ጥቅምት 2017 ዓ.ም

በጽሁፉ ውስጥ የተካተቱት ቁምነገሮች የመጀመሪያ ደረጃ ምልከታ ምዝገባ ተብለው ከሚጠቀሱት የታሪክ ማጣቀሻ ማስረጃዎች ውስጥ የሚካተቱ ናቸው።
በስነ-ጽሁፍ አቀራረብ ረገድ በወቅቱ የነበረውን የጦማር አጻጻፍ ስልት አጉልቶ በማሳየት በዘመናት መካከል የተፈጠረውን የደብዳቤ እንዲሁም ታሪክ አዘጋገብ የእድገት ወይም ውድቀት ደረጃ አጉልቶ የሚያሳይ በመሆኑ ለስነጽሁፍ ተመራማሪዎች የሚሰጠው ፋይዳ ቀላል አይሆንም።
ከታሪክ አንጻር የወሰድነው እንደሆነ በወቅቱ የተሟላ ማስረጃ ያልተገኘላቸውን እውነታዎች ለህብረተሰባችንና ለታሪክ ተመራማሪዎች በመስጠቱ ረገድ የላቀ አስተዋጻኦ ይኖረዋል:: በዋናነትም የግለታሪክ ዘጋቢው በኩነቱ ወቅት እርምጃው በተወሰደባቸው ቀናት ውስጥ ተሳታፊ የነበሩ በመሆናቸው በአይናቸው የተመለከቱትን የዘገቡ በመሆኑ ከዚህ በፊት ኩነቱን አስመልክቶ የተጻፉ የጥናትና ምርምር ስራዎች ጉድለት በማሟላቱ ረገድ ፋይዳው የጎላ ነው።
የሰምና ወርቅ መጽሔት አዘጋጅዎች

ሳይንስ, ባህል, ታሪክ

የባህል መድኃኒቶች በተለያዩ የዓለም ክፍሎች እና የመድኃኒት ዕፅዋት እንክብካቤ አስፈላጊነት በኢትዮጵያ -(በቅርብ ጊዜ ታትሞ ከወጣው የመጻሕፍት ስብስቦች የተቀዳ) -(ዶ/ር ፈቃዱ ፉላስ)

ኢትዮጵያ በርካታ የብዝሃ ህይወት ሀብቶች አሏት። የባህል መድኃኒት ዕፅዋት ቁጥራቸው እየመነመነ መሄድ፣ በተለይም የመድኃኒት ዕውቀት ያላቸው አረጋውያን ዕልፈተ-ሕይወት አሳሳቢ መሆኑን ኢትዮጵያውያን አጥኚዎች… ጠቁመዋል። ከዚህም ጋር ተያይዞ በልዩ ልዩ ምክንያቶች መላ ማህበረሰቦች ከጊዜ ወደ ጊዜ መፈናቀላቸው፣ የመድኃኒት አዋቂዎች በዕድሜ መግፋትና ወጣቱ ትውልድ ከአረጋውያኑ ለመማር ፈቃደኛ አለመሆኑ ይህን ጠቃሚ ባህል የማቆየቱና የማስተላለፉን ችግር አባብሶታል። የደን መራቆት ትልቅ ችግር አስከትሏል።

ታሪክ, የሕይወት ታሪክ, ጥናትና ምርምር

የሻምበል ሲስተር አስቴር አያና አጭር የሕይወት ታሪክ ከልጃቸው ከያፌት አስራት – ነሐሴ ፲፪, ፳፻፲፭ (August 18, 2023)

የተባበሩት መንግስታት ዋና ጸሐፊ ዳግ ሃመርሾልድ ለግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የላኩት ቴሌግራም:- “ስሟን ገና ያላወቅነው አንዲት ኢትዮጵያዊት ነርስ አንድ አሜሪካዊ መኮንን በአንድ ጂፕ መኪና ውስጥ ተይዞ ሲደበደብ ብቻዋንና ባዶ እጅዋን ልታድነው በሙሉ ልበኝነት ሞክራ ሳይሆንላት ቢቀር ኮንጎዎቹ አሜሪካኑን ይዘዉት ሲሄዱ ሰፈራቸው ድርስ ተከትላ ሔደች፡፡ እዚያም በጥይት ሊገድሏት ቢያስፈራሯትም ተመልሳ ወሬውን ለኢትዮጵያውያኑ ነግራ ሶስቱን አሜሪካውያን አድነዋቸዋል፡፡”  ንጉሡ በመልሳችው ለሲስተር የላኩት መልእክት ” ሥራሽ  ላይ ሆነሽ በፈጸምሸው መልካም ተግባር በጣም ተደስተናል፡፡ ስለ መልካም ሥራሽና ስለ መልካም አደራጎትሽ በጣም እናመሰግንሻለን” ብለው ነበር፡፡ ሲስተርም  በትህትና ሲመልሱ  “ላደርገው የሚገባኝን አገልግሎት በመፈጸሜ የግርማዊነትዎ የምስጋና ቴሌግራም ስለ ደረሰኝ ፤ አነስተኛ አገልጋይዎን በምስጋና ላሰበኝ ግርማዊነትዎ እድሜ በመለመን መሬት እስማለሁ” በማለት ነበር ፡፡

ሀይማኖት, ሥነጽሑፍ, Uncategorized

ስለኢትዮጵያ፡ደራሲያን።

ጽሑፉ፡የፕሮፌሰር፡ታምራት፡አማኑኤል፡ነው። ፕሮፌሰር፡ታምራት፡ከሰማንያ፡ዓመታት፡በፊት፡በትምርትና፡ሥነጥበብ፡ሚኒስቴር፡አማካሪ፡ኾነው ይሠሩ፡ነበር። ነገር፡ግን፡በዚያን፡ጊዜ፡ፕሮፌሰር፡በመባል፡ፈንታ፡ሊቀማእምራን፡ይባሉ፡ነበር። ፕሮፌሰሩ ሲናገሩም :- “ባ፩ኛው፡ዘመን፡በዐማርኛ፡የተጻፈው፡ሥራ፡ እጅግ፡ጥቂት፡ነው።የተጻፈውም፡ላንዳንድ፡ነገሥታት ምስጋና፡ደራሲው፡ካልታወቀ፡የተገጠመ፡ቅኔ፡ነው። ቅኔውም፡በዘመናት፡ውስጥ፡አንድ፡ቋንቋ፡እንደምን፡ ኹኖ፡እየተለዋወጠ፡ለመኼዱ፡ዋና፡ምስክር፡ከመኾኑ በላይ፣በዚያ፡ዘመን፡የነገሥታቱ፡ሥልጣንና፡የተዘረጋበት፡የሰፊው፡አገር፡ኹኔታ፡እንዴት፡እንደነበረ፣ለታ ሪክና፡ለዦግራፊም፡ማስረጃ፡ለመኾን፡ይረዳል። ዐማርኛው፡ዛሬ፡ዘመን፡የማንናገርበትና፡የማንጽፈው፣ለማስተዋሉም፡የሚያስቸግረንና፡የሰዋስው፡አካኼድ፡የተለዋወጠ፡ብዙ፡ቃልና፡አገባብ፡አለበት። እርሱን፡የመሰለ፡ዐማርኛም፡በየዘመኑ፡እየተጻፈ፡ምናልባት፡እስከ፡ ፲፭፻፺፱-፲፮፻፯፡ደርሶ፡ ይኾናል።”

ሥነጽሑፍ, የሕይወት ታሪክ, ጥናትና ምርምር

የአቶ ሰይፉ መታፈሪያ የሥነግጥም መድብሎች የጥናት እና የምርምር ሥራዎች ።

ገጣሚ ሲቆጣ (ሰይፉ መታፈሪያ)፣
መጻፍ፣ መጻፍ አለኝ ማቅለም ወረቀት፣ ብእሬን ማስቆጣት ቀይ ደም ማስተፋት።

ዕውቁ ገጣሚ፣ መምህር እና የፎክሎር ባለሙያ ሰይፉ መታፈሪያ ፍሬው በርካታ ያገራችንን እና የአውሮጳን ቋንቋዎች አጥርተው የሚናገሩ እና ጠንቅቀው የሚያውቁ ልሳነ ብዙ ምሁርና ተመራማሪ ናቸው። በኢትዮጵያ እጅግ የተለየ የግጥም አጻጻፍ ስልትን ያስተዋወቁና ያስፋፉ ዕውቅ ገጣሚ ናቸው። እሳቸው እንደሚሉት የግጥማቸው የአጻጻፍ (ዓይነት) „በብዙ ረገድ ባህል-ከተል አይደለም። በዚህ ያጻጻፍ አዲስነት አስገዳጅነትም ስም ስላስፈለገው „ስንኝ አጠፍ ግጥም“ የሚል ስያሜ ሰጥተውታል። ላለፉት ሃምሳ ዓመታት በሀገራችን ቁጥራቸው በርካታ የሆኑ የፎክሎር እና የሥነ ጽሑፍ ተማሪዎችን እና ምሁራንን አፍርተዋል።

ሥነጽሑፍ, ታሪክ, ጥናትና ምርምር

አውሮጳ እና ኢትዮጵያ፤ አመራርና የሥልጣኔ ፖለቲካ

በዘመነ መሳፍንት ስድሳ አምስት ዓመት ሙሉ በማይረባ ምክንያት የተከፋፈለውን፣ የዘቀጠውን፣ የባለገውን ህዝባችንን ከወደቀበት መቀመቅ አውጥተው ኢትዮጵያን ወደጥንት ታላቅነቷ ለመመለስ የኢትዮጵያን ነገሥታት፣ መጀመሪያ አፄ ቴዎድሮስ፣ ቀጥሎ አፄ ዮሐንስ በኋላም አፄ ምኒልክ ያውሮጳን መንግሥታት ድጋፍና ወዳጅነት አጥብቀው ይፈልጉ፣ ይማጠኑ ነበር። አውሮጳውያን ግን የሚፈልጉት የኢትዮጵያን ውድቀቷን፣ ክፍፍሏን፣ ንብረቷንና መሬቷን እንጅ የሕዝቧን ነፃነትና ብልጽግና ስላልነበር በነዚህ ቅን ነገሥታቶች ላይ በየጊዜው ተደጋጋሚ አሳፋሪ ሸርና ተንኮል፣ ሴራና ተራ ማጭበርበር ይፈጽሙባቸው ነበር።

ሥነጽሑፍ, ባህል

መጽሐፈ ምሳሌ ዘጨዋ ተረት  

ይህ መጽሐፍ ያልታተመና በዩናይትድ ስቴትስ የኮንግሬስ ቤተመጻሕፍት ውስጥ በአፍሪካና በመካከለኛው ምሥራቅ ዋና ክፍልየኢትዮጵያና የኤርትራ ሃገራት የመጻሕፍት ክምችት ክፍል ውስጥከሌሎች ካልታተሙ የግእዝ፣ የአማርኛና የትግርኛ መጻሕፍት ጋርይገኛል። የተጻፈው በ1911 ዓ.ም ሲሆን ተረቶቹን በጽሑፍያሰፈረው የንጉሥ ወልደጊዮርጊስ አሽከር ነኝ የሚለው ነጋዴው አቶአበሩ የተባለ  የማጂ ከተማ ነዋሪ ሰው ነው። ይህን ያጠናቀረውንየጥንት ተረት መድብል ለወዳጁ  ለእንግሊዝ መንግሥት መኮንንለሜጀር አጥሒል [Major Athil] ሲያበረክት በመጽሐፉ ላይ ተጽፎእንደተገኘው፣ “ ይህን እያዩ እንዲያስታውሱኝ” ከሚል ማሳሰቢያ ጋርነበር። በዚህ መድብል ውስጥ በወረቀት ላይ ተጽፈው የተገኙተረቶች አስራ ሁለት ያህል ናቸው።

ሀይማኖት

የኢትዮጵያውያን ገዳምና ተማሪ-ቤት በቫቲካን፤ ግርማይ ተስፋጊዮርጊስ፤ ሰሜን አሜሪካ (ጥር 2012 ዓም)

ኢትዮጵያውያን ነጋድያን (ፕልግርምስ) ከአስራ አምስተኛ ክፍለዘመን ጀምረው የቅዱስ ጴጥሮስና የቅዱስ ጳውሎስ መቃብር ለመሳለም ወደ ሮም ይሄዱ እንድነበረ በቫቲካን መዛግብትና በኣንዳኣንድ የታሪክ ጸሓፊዎች ሰነዶች ተጽፎ ይገኛል። የሮም ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ለነዚህ ነጋድያን በቫቲካን ውስጥ የሚገኝ የትልቁ ቅዱስ ኢስጢፋኖስ ገዳም የሚባል ጥንታዊ ቤተክርስቲያን ከነ እንግዳ መኖርያ ቤት ሰጡዋቸው። ይህ ቤተክርስቲያን ለኢትዮጵያውያን ከተበረከተ በኋላ Santo Stefano Dei Mori “የቀይ ዳማዎች ቅዱስ ኢስጢፋኖስ” ተባለ። ከዛን ጊዜ ጀምሮ ይህ ቦታና ገዳም በኢየሩሳሌም በኩል ወደ ሮም ይሄዱ የነበሩ ኢትዮጵያውያን መነኮሳት ንብረት ሆኑ። መነኵሴዎቹ ከየትኞች የኢትዮጵያ ገዳሞች ይመጡ እንደነበረ ሁሉ በቫቲካን መዛግብት ተጽፎ ይገኛል። ደብረ-ዳሞ፣ ደብረ-ሊባኖስ፣ ደብረ-ቢዘን ወዘተ ለምሳሌ ሊጠቀሱ ይችላሉ፡፡ ይህ ከፍ ያለ ክብርና ታሪክ ያላት ብቸኛ ኣንዲት ኮሌጅ በቫቲካን ውስጥ መኖር ለኢትዮጵያ ህዝብ ትልቅ ክብር ነው። ስለዚህም የኢትዮጵያ ታልላቅ ሰዎችና ባለስልጣናት ወደ አውሮጳ ሲሄዱ ይህችን ኮሌጅ ሳይጎበኙ አያልፉም ነበር። ለምሳሌ ቀዳማዊ ኃይለስላሴ ሁለት ጊዜ፣ (አልጋውራሽ እያሉ በ1924 እና ንጉሠ-ነገሥት እያሉ በ1970 ዓ ም) ፥ ልዕልት ተናኘ ወርቅና ልዑል አስፍሓ ወሰን በ1932 ዓ. ም. በቅርቡም ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በ2019 ወዘተ. ይገኙበታል።

ታሪክ

ወይዘሮ ሲልቪያ ፓንከርስት እንግሊዛዊቷ የኢትዮጵያ ጀግና፤ ኪዳኔ ዓለማየሁ ፤ ሰኔ 18 ቀን 2011 ዓ/ም

ይህ አጭር ጽሑፍ (1) የሚያተኩረው፤ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን፤ ወለተ ክርስቶስ ተብላ በተሰየመችው፤ የዓለም ስሟ ሲልቪያ ፓንከርስት በሆነው፤ ኢትዮጵያ በፋሺሽቶች በተወረረችበት ጊዜ፤ ከዚያም በሁዋላ ሌሎች ቅኝ ገዢዎች ሊቀራመቷት በቋመጡበት ዘመን በሚያስደንቅ ጀግንነት 20 ዓመት ሙሉ በታገለችው፤ በተከበረች፤ ወይዘሮ የሕይወት ታሪክ ላይ ነው።

ሲልቪያ ፓንከርስት፤ እ.ኤ.አ በ1882 እንግሊዝ ሐገር ተወልዳ፤ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየችው፤ እ.ኤ.አ መስከረም 27 ቀን 1960 አዲስ አበባ ነበር። አስከሬኗ የተቀበረውም፤ ወለተ ክርስቶስ ተሰኝታ፤ እንደ ሌሎች ታላላቅ አርበኞች፤ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ፤ ልዑል አልጋ ወራሽ አስፋ ወሰንና ሌሎች ክቡራን በተገኙበት በቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ነበር። የ50ኛው ዓመት መታሰቢያዋ መስከረም 17 ቀን 2003 ዓ/ም በቅድስት ሥላሴ ቤ/ክ ተከብሯል።

ሀይማኖት

የአስማት ጸሎት (ሳዶር አላዶር) ጌታቸው ኃይሌ ኒው ዮርክ ከተማ፤ ዩናይትድ ስቴትስ ሚያዝያ 15 ቀን 2011 ዓ.ም

በባህል ሲወርድ ሲዋረድ እንደደረሰን፥ አይሁድ ክርስቶስን ሲሰቅሉት በአምስት ምስማሮች (ችንካሮች) ቸንክረውት ነበር። እነዚህ ምስማሮች (ችንካሮች) በግሪክኛ ስም አላቸው፤ (1) ሳዶር፥ (2) አላዶር፣ (3) ዳናት፥ (4) አዴራ፥ (5) ሮዳስ ይባላሉ። እነሱንም የችንካሮቹ ስሞች እንደሆኑ ከማቆየት አልፈው፥ የአምላክ የምስጢር ስሞች ከሚሏቸው አስማት ጋራ ደባልቀው፥ ለመፍትሔ ሥራይ (መርዝና ድግምት ማርከሻ መዳኒት) የጸሎት ክፍል አደረጓቸው።

ሥነጽሑፍ

የኢትዮጵያ ጊዜያዊ ሁኔታና የመንፈሳዊ ፖለቲካ ራዕይ ከፈንታሁን ጥሩነህ (ዋሺንግተን ዲ.ሲ)

ሰኔ ወር 2010 ዓ.ም ጀምሮ በኢትዮጵያ ምድር የሚካሄደው የለውጥ ነፋስ አዲስና አስገራሚ ነው። በእግዚአብሔር ማመን ተስፋ አስቆርጧቸው የነበሩ ሁሉ ተገርመው የዶክተር አቢይ አህመድ አሊ በፖለቲካው መስክ መነሳት ላይ “የእግዚአብሔር እጅ አለበት” እስኪሉ ድረስ ሁኔታው ማራኪ ሆኖ ይገኛል። በምዕራቡና በምሥራቁ ዓለም የፖለቲካ ንድፈ-ሃሳቦችና ጽንሰ-ሃሳቦች የተራቀቁ ኢትዮጵያውያን ምሁራን በሁኔታው በመደመም የሚሉት አጥተው ዝምታን የመረጡበት ጊዜ ነው። አንዳንድ ዜጎች ደግሞ ይህ ክስተት ጊዜያዊ ቅዠት እንጂ እውን አይደለም በማለት ያላቸውን ግራሞት ይገልጻሉ። እኔ በበኩሌ በዶክተር አህመድ አሊ የሚመራው አዲሱ ፖለቲካ ሲጠበቅ የነበረው የእግዚአብሔር ጣልቃ ገብነት ያስከተለው መሆኑን አምናለሁ። ይህ እምነቴ ደግሞ ይህን መጣጥፍ እንድጽፍ ምክንያት ሆኖኛል።

ባህል, ታሪክ, ፖለቲካ

ያላዩት አገር ሲናፍቅ፥ የአዲስ መንግሥት ምኞት (ጌታቸው ኃይሌ)

“መቆየት መልካም ነው፤ የቆየ ሰው የማይሆን ነገር ሲሆን ያያል” ይባላል። ከማይሆኑ ነገሮች አንዱ ያላዩት አገር መናፈቅ ነው። ስለዚህ፥ “ያላዩት አገር አይናፍቅም” ይባላል። መቆየት መልካም ነው፥ እኔም ያላየሁት አገር እስኪናፍቀኝ ቆይቻለሁ። ግን የናፈቀኝ አዲስ ነገር ቢሆንም በኔ አልተጀመረም፤ መንፈሳውያን አባቶቻችንም ናፍቀውታል።

Scroll to Top