“ከታሪክ ገጽ” (ጌታቸው ኃይሌ)
“በዚህ ዓምድ በሰፊው ሊታወቁ የሚገባቸው የመሰሉንን አንዳንድ ጥንታዊ ታሪክ የያዙ ሰነዶችን ለማቅረብ እንሞክራለን።”
“በዚህ ዓምድ በሰፊው ሊታወቁ የሚገባቸው የመሰሉንን አንዳንድ ጥንታዊ ታሪክ የያዙ ሰነዶችን ለማቅረብ እንሞክራለን።”
“ፊደሎች ጥንት እንደተፈጠሩ በነባርነት ሊኖሩ አይችሉም። ወረታቸው ያልፍና ለዛቸውን ያጣሉ። በዚያን ጊዜ አንዳንድ ታታሪዎች ወይም ደርጅቶች እየተነሱ ክብደታቸውንና አስቸጋሪነታቸውን እየገመገሙ አጣጣላቸውም ሆነ ቅርፃቸው ለጽሕፈት እንዲያመችና ለትምህርት እንዲቀል ማሻሻያ አሳቦችን ያበረክቱላቸዋል።”
“በላይ ዘለቀ የተለመደውን የኢትዮጵያ መሪዎችን እንቢተኛነቱን በማክረሩ እንደ ወንጀለኛ ሲሰቀል የመጨረሻ ቃሉ ከአንደበቱ የወጣው “አንቺ አገር ወንድ ልጅ አይውጣብች“ ነበር።”
“የዚህ ድርጅት ዋና ዓላማ በሳይንስና ቴክኖሎጂ ጥናትና ምርምር የሚያካሂድና የሚያቀናጅ ስለሚሆን በተለይም ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ የሳይንስ ምሁራን በውጭ ከሚገኘው ኢትዮጵያዊ የሳይንስ ሙያተኛ ጋር ተገናኝተው የጥናትና ምርምር ተለምዶ የሚለዋወጡበትና የሚረዳዱበትን መንገድ የሚፈልጉበት መንኮራኩር መሆን ነው።”
“ያ ለካፊ ሙስሊኒ ሳይቸግረው ለከፈውና ነው እንጅ አፈ ቄሣር ባይሆንማ ኖሮ ለአፈ ወርቅ ሥነጽሑፍ ምን ሰሀ ይወጣለት ነበር?”
“ያቺ አህያም በበኩሏ፣ ከማን አንሳለሁ ብላ፤
ሥጋ መመገብ ጀምራለች፣ ሠርዶ መኖዋን ጥላ።”