ሥነጽሑፍ, ባህል

ሌስላውን ዘረፋ – አጭር የምርምር ማስታወሻ

ይህ አጭር ማስታወሻ የሴማዊ ቋንቋዎች ጥናት አባት ተብለው የሚታወቁት ዎልፍ ሌስላው (Wolf Leslau) በ1961 የዐማርኛ የገደል ማሚቶ ጥምር ቃላት የተሰኘውን መጣጥፋቸውን ለመቃኘትና እውቅና ለመስጠት በአቶ ዳናኤል አበራ ተዘጋጅቶ ቀርቦአል። ሌስላው በጥናቱ ላይ 80 ጥምር ቃላቶችን በመለየት በማሳያነትም እንደ አርቲ ቡርቲ …እንቶ ፈንቶ የሚሉትንና “ምንም ቁም ነገር የለውም… የማይረባ ነው…” ለማለት የሚጠቅሙትን ገልጸዋል። በአሁኑ ጊዜ ከእነዚህ 80 ጥምር ቃላት መካከል 25ቱ ጥቅም ላይ የዋሉ ሲሆኑ 11 ቃላትን አቅራቢው ጨምረዋል ። እነዚህ አስተጋቢ ቃላቶች ከ6 ሚሊዮን የአማርኛ ቃላት ጋር ተጣጥመው ተገኝተዋል።