የባህል መድኃኒቶች በተለያዩ የዓለም ክፍሎች እና የመድኃኒት ዕፅዋት እንክብካቤ አስፈላጊነት በኢትዮጵያ -(በቅርብ ጊዜ ታትሞ ከወጣው የመጻሕፍት ስብስቦች የተቀዳ) -(ዶ/ር ፈቃዱ ፉላስ)

ኢትዮጵያ በርካታ የብዝሃ ህይወት ሀብቶች አሏት። የባህል መድኃኒት ዕፅዋት ቁጥራቸው እየመነመነ መሄድ፣ በተለይም የመድኃኒት ዕውቀት ያላቸው አረጋውያን ዕልፈተ-ሕይወት አሳሳቢ መሆኑን ኢትዮጵያውያን አጥኚዎች… ጠቁመዋል። ከዚህም ጋር ተያይዞ በልዩ ልዩ ምክንያቶች መላ ማህበረሰቦች ከጊዜ ወደ ጊዜ መፈናቀላቸው፣ የመድኃኒት አዋቂዎች በዕድሜ መግፋትና ወጣቱ ትውልድ ከአረጋውያኑ ለመማር ፈቃደኛ አለመሆኑ ይህን ጠቃሚ ባህል የማቆየቱና የማስተላለፉን ችግር አባብሶታል። የደን መራቆት ትልቅ ችግር አስከትሏል።

መጽሐፈ ምሳሌ ዘጨዋ ተረት  

ይህ መጽሐፍ ያልታተመና በዩናይትድ ስቴትስ የኮንግሬስ ቤተመጻሕፍት ውስጥ በአፍሪካና በመካከለኛው ምሥራቅ ዋና ክፍልየኢትዮጵያና የኤርትራ ሃገራት የመጻሕፍት ክምችት ክፍል ውስጥከሌሎች ካልታተሙ የግእዝ፣ የአማርኛና የትግርኛ መጻሕፍት ጋርይገኛል። የተጻፈው በ1911 ዓ.ም ሲሆን ተረቶቹን በጽሑፍያሰፈረው የንጉሥ ወልደጊዮርጊስ አሽከር ነኝ የሚለው ነጋዴው አቶአበሩ የተባለ  የማጂ ከተማ ነዋሪ ሰው ነው። ይህን ያጠናቀረውንየጥንት ተረት መድብል ለወዳጁ  ለእንግሊዝ መንግሥት መኮንንለሜጀር አጥሒል [Major Athil] ሲያበረክት በመጽሐፉ ላይ ተጽፎእንደተገኘው፣ “ ይህን እያዩ እንዲያስታውሱኝ” ከሚል ማሳሰቢያ ጋርነበር። በዚህ መድብል ውስጥ በወረቀት ላይ ተጽፈው የተገኙተረቶች አስራ ሁለት ያህል ናቸው።

ያላዩት አገር ሲናፍቅ፥ የአዲስ መንግሥት ምኞት (ጌታቸው ኃይሌ)

“መቆየት መልካም ነው፤ የቆየ ሰው የማይሆን ነገር ሲሆን ያያል” ይባላል። ከማይሆኑ ነገሮች አንዱ ያላዩት አገር መናፈቅ ነው። ስለዚህ፥ “ያላዩት አገር አይናፍቅም” ይባላል። መቆየት መልካም ነው፥ እኔም ያላየሁት አገር እስኪናፍቀኝ ቆይቻለሁ። ግን የናፈቀኝ አዲስ ነገር ቢሆንም በኔ አልተጀመረም፤ መንፈሳውያን አባቶቻችንም ናፍቀውታል።

“የአንድ ኢትዮጵያዊ ደራሲ ሕመም” (እንዳለጌታ ከበደ)

በዚህ ዘመን ያለ አንድ ኢትዮጵያዊ ደራሲ በአብዛኛው ራሱ ጽፎ፣ ራሱ አርሞ፣ ራሱ አስተይቦ፣ ራሱ ፊደል ለቅሞ፣ ራሱ ማተሚያ ቤት ፈልጎ፣ ራሱ አሰራጭቶ፣ ራሱ ማስተዋወቂያ ሠርቶ፣ ራሱ አስመርቆ፣ ራሱ ለኅትመት ያወጣውን ገንዘብ ሰብስቦ፣ … ይኖራል። ብዙ ነው ድካሙ።

“የግማደ መስቀል ወደ ኢትዮጵያ መምጣት” (ጌታቸው ኃይሌ)

የግማደ መስቀል መገኘት በብዙ ታሪክ ተመዝግቧል። ይህ ጽሑፍ እንደሚያሳየው፥ ከእኛ ዘንድ የተገኘው ታሪክ በሁለት ነገር ይለያል። አንደኛ፦ መስቀሉን አፈላልጋ ስላገኘችው ስለ ንግሥት እሌኒ ታሪክ የሚነገረው ከሌላ ዘንድ የሌለ ሰፋ ያለና ሲያነቡት የሚጥም ነው። ሁለተኛ፦ ስለግማደ መስቀሉ ወደ ኢትዮጵያ መምጣት ብዙ የታሪክ ሰነዶች መስክረዋል።

ባህልና ሕዝብ (ይርጋ መንግሥቱ እስጢፋኖስ)

የዛሬይቱ ኢትዮጵያ ከ81 (ሰማንያ አንድ) በላይ የሆኑ የብሔር፣ የብሔረሰብና የማህረሰብ ቅንብር ያላት መሆኑ ግልጽ ነው። በመቶዎች የሚቆጠሩ አባላት ብቻ ከአላቸው ባህላቸውና የዝርያቸው ሐረግ ሊዋጥና – ጨርሶም ሊጠፋ ጥቂት ከቀራቸው ማህበረሰቦች አንስቶ፣ ብዙ ሚሊዮን አባላት እስከ አሏቸው አያልና ሠፋፊ መሬት እስከ ያዙት የኦሮሞና የአማራ ብሔሮች ባህሏን የሚያበለጽጉና ሕብረሰባዊነቷን የሚያጠናክሩ፣ ሕብሯን የሚያሞሽሩ ህዝቦች የሚኖሩባት አገር ነች።

ባህል ሥነጽሑፍና ኪነጥበብ

በኢትዮጵያ ከየብሔረሰቡ የሚፈልቁ ብዙ አሸብራቂና አስደሳች ትርጉም የሚሰጡ የባሕል ቅርሶች አሉ ። ብዙ ዓይነት ጣዕመ ዜማ ያላቸው የሙዚቃ መሳሪያዎችም ቁጥራቸው በርካታ ነው። ብሔራት የባህላቸውን ምንነት የሚገልጹባቸው የራሳቸው የሆነ የስእልና የቅርጻ ቅርጽ አቀራረጽ አሳሳልና ልዩ ልዩ ብልሃት ሞልቷል። ይህ ሁሉ አስደናቂ ነገር አብይ ቅርስ ስለሆነ ይህ ትውልድ የራሱ የሆነውን ቅርሳዊ ሃብት ኮርቶበት ለመጪው ትውልድ በቂ መሰረት ለማቆየት አካባቢውን አጥንቶና መርምሮ ማወቅና ማሳወቅ ማቆየት ይገባዋል።