የባህል መድኃኒቶች በተለያዩ የዓለም ክፍሎች እና የመድኃኒት ዕፅዋት እንክብካቤ አስፈላጊነት በኢትዮጵያ -(በቅርብ ጊዜ ታትሞ ከወጣው የመጻሕፍት ስብስቦች የተቀዳ) -(ዶ/ር ፈቃዱ ፉላስ)

ኢትዮጵያ በርካታ የብዝሃ ህይወት ሀብቶች አሏት። የባህል መድኃኒት ዕፅዋት ቁጥራቸው እየመነመነ መሄድ፣ በተለይም የመድኃኒት ዕውቀት ያላቸው አረጋውያን ዕልፈተ-ሕይወት አሳሳቢ መሆኑን ኢትዮጵያውያን አጥኚዎች… ጠቁመዋል። ከዚህም ጋር ተያይዞ በልዩ ልዩ ምክንያቶች መላ ማህበረሰቦች ከጊዜ ወደ ጊዜ መፈናቀላቸው፣ የመድኃኒት አዋቂዎች በዕድሜ መግፋትና ወጣቱ ትውልድ ከአረጋውያኑ ለመማር ፈቃደኛ አለመሆኑ ይህን ጠቃሚ ባህል የማቆየቱና የማስተላለፉን ችግር አባብሶታል። የደን መራቆት ትልቅ ችግር አስከትሏል።

የሻምበል ሲስተር አስቴር አያና አጭር የሕይወት ታሪክ ከልጃቸው ከያፌት አስራት – ነሐሴ ፲፪, ፳፻፲፭ (August 18, 2023)

የተባበሩት መንግስታት ዋና ጸሐፊ ዳግ ሃመርሾልድ ለግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የላኩት ቴሌግራም:- “ስሟን ገና ያላወቅነው አንዲት ኢትዮጵያዊት ነርስ አንድ አሜሪካዊ መኮንን በአንድ ጂፕ መኪና ውስጥ ተይዞ ሲደበደብ ብቻዋንና ባዶ እጅዋን ልታድነው በሙሉ ልበኝነት ሞክራ ሳይሆንላት ቢቀር ኮንጎዎቹ አሜሪካኑን ይዘዉት ሲሄዱ ሰፈራቸው ድርስ ተከትላ ሔደች፡፡ እዚያም በጥይት ሊገድሏት ቢያስፈራሯትም ተመልሳ ወሬውን ለኢትዮጵያውያኑ ነግራ ሶስቱን አሜሪካውያን አድነዋቸዋል፡፡”  ንጉሡ በመልሳችው ለሲስተር የላኩት መልእክት ” ሥራሽ  ላይ ሆነሽ በፈጸምሸው መልካም ተግባር በጣም ተደስተናል፡፡ ስለ መልካም ሥራሽና ስለ መልካም አደራጎትሽ በጣም እናመሰግንሻለን” ብለው ነበር፡፡ ሲስተርም  በትህትና ሲመልሱ  “ላደርገው የሚገባኝን አገልግሎት በመፈጸሜ የግርማዊነትዎ የምስጋና ቴሌግራም ስለ ደረሰኝ ፤ አነስተኛ አገልጋይዎን በምስጋና ላሰበኝ ግርማዊነትዎ እድሜ በመለመን መሬት እስማለሁ” በማለት ነበር ፡፡

አውሮጳ እና ኢትዮጵያ፤ አመራርና የሥልጣኔ ፖለቲካ

በዘመነ መሳፍንት ስድሳ አምስት ዓመት ሙሉ በማይረባ ምክንያት የተከፋፈለውን፣ የዘቀጠውን፣ የባለገውን ህዝባችንን ከወደቀበት መቀመቅ አውጥተው ኢትዮጵያን ወደጥንት ታላቅነቷ ለመመለስ የኢትዮጵያን ነገሥታት፣ መጀመሪያ አፄ ቴዎድሮስ፣ ቀጥሎ አፄ ዮሐንስ በኋላም አፄ ምኒልክ ያውሮጳን መንግሥታት ድጋፍና ወዳጅነት አጥብቀው ይፈልጉ፣ ይማጠኑ ነበር። አውሮጳውያን ግን የሚፈልጉት የኢትዮጵያን ውድቀቷን፣ ክፍፍሏን፣ ንብረቷንና መሬቷን እንጅ የሕዝቧን ነፃነትና ብልጽግና ስላልነበር በነዚህ ቅን ነገሥታቶች ላይ በየጊዜው ተደጋጋሚ አሳፋሪ ሸርና ተንኮል፣ ሴራና ተራ ማጭበርበር ይፈጽሙባቸው ነበር።

የዳግማዊ አጼ ቴዎድሮስ የሕይወታቸው መጨረሻ ሰዓት እና የመቅደላ ዝርፊያ

ይህ ታሪክ፣ በ1874 [1866 ዓ.ም]  ሄንሪ ኤም. እስታንሊ የተባለው የኒውዮርክ  ሄራልድ ጋዜጣ ተቀጣሪ  እንደ አውሮፖ አቆጣጠር በ1868 በጄኔራል ሮበርት ናፕዬር የተመራው የእንግሊዝ ጦር ጋር ወደ ኢትዮጵያ  በመጓዝ ያከናወነውን “ኮማሲ እና መቅደላ” በተሰኘው የሚመስጥ መጽሐፉ የመዘገበው ነው። ይህ አጭር ጽሑፍም የተጻፈው የንጉሡን ሕይወት ማለፍ ተከትሎ እስታንሊ በገጽ  449-464 ያሰፈረውን ሀተታ ማስረጃ  መሰረት በማድረግ ነው። በተጨማሪም በእውን ያያቸውን ከመቅደላ የተዘረፉትን ቅርሶች ገጽ 454-462 በዝርዝር ያስቀምጣል። የእንግሊዝ ጦር ወደ ኢትዮጵያ የዘመተበት ምክንያት ንጉሡ ለንግሥት ቪክቶሪያ የሁለቱ ሃገራት ወዳጅነት መመስረት እና መጠናከር በተመለከተ ለጻፉላቸው ደብዳቤ መልስ ስለተነፈጋቸው፣ በአጸፋው ያሰሯቸውን የእንግሊዝ መልክተኞች ከእስር ለማስፈታት መሆኑ ሊታወስ ይገባል።

የዐፄ ካሌብ ወይም የቅዱስ ኤልስባን* ገድል

ዐፄ  ኢዛና  ሃሌን ንጉሠ ነገሥት 
ዘኢትዮጵያ ተብሎ አስር ዓመት 
ከገዛ በኋላ ከልጆቹ መሃል የአክሱም 
መኳንንት ካሌብን አነገሡ፤ 
ስመ ንግሡም ዳግማዊ 
ዓፄ እለ አጽብሃ ንጉሠ ነገሥት 
ዘኢትዮጵያ መሲሃ እግዚአብሔር 
ተብሎ በ483 ዓም ነገሠ።
ሰላሳ አምስት ዘመን ከገዛ በኋላ 
ሃይማኖቱ ኦሪታዊ የሆነ ዱኖባስ 
ፊንሐስ በናግራን [አሁን የመን 
ተብሎ በሚታወቀው] 
የክርስቲያኖች ቁጥር መብዛቱን 
አይቶ በግዛቱ ውስጥ የነበሩትን 
ከአራት ሺ በላይ ክርስቲያኖችን  
የገደለውን ንጉስ በማስወገዱ 
ይታወቃል። 

ኢትዮጵያ፤ የአባይ ወንዝ ባለቤትነትና ተጠቃሚነት ጥያቄ ፤ ኪዳኔ ዓለማየሁ ፤ መስከረም 2012

በጥንቱ ዘመን፤ የአባይ ወንዝ ዋናዋ ምንጭ ኢትዮጵያ መሆኗና ባለቤትነቱዋ ታውቆ፤ የግብጽ መሪዎች በየዓመቱ ለሚጎርፍላቸው ውሀ ይከፍሉ ነበር። በቅርቡ በየድረ-ገጹ በስፋት ከሚቀርቡት ሐተታዎች፣ ትችቶችና አስተያየቶች ውስጥ ሰፊ ስፍራ ይዞ የሚገኘው አንደኛው አርእስት ኢትዮጵያ ውስጥ በመገንባት ስላለው ታላቅ የአባይ ግድብ ነው። ስለ ግድቡ የተንጸባረቁት የተለያዩ አስተያየቶች እንዳሉ ሆነው የአባይ ወንዝ ባለቤትነት የማን እንደ ሆነና በጋራ ተጠቃሚነት ዙርያ ውሱን በሆነ መንገድ ተነካ እንጂ በጥልቀት በተከናወነ ምርመራና በዓለም-አቀፍ ሕግ በተመሠረተ አስተማማኝ ማስረጃ የተደገፈ ጽሑፍ አልቀረበም። የዚች ጦማር ዓላማም ኢትዮጵያ ከሱዳንና ከግብጽ ጋር እንዲሁም ከሌሎች የአባይ ተፋሰስ ሀገሮች ጋር  በምታከናውናቸው ውሎች ያሁኑንና የመጪውን ትውልድ እንዲሁም የሌሎች ሀገሮችን መብት በሚጠብቅ ሥልት መጠቀሟን እንድታረጋግጥ ተገቢውን ቅድመ-ዝግጅትና ጥንቃቄ እንድታደርግ ለማሳሰብ ነው።

ወይዘሮ ሲልቪያ ፓንከርስት እንግሊዛዊቷ የኢትዮጵያ ጀግና፤ ኪዳኔ ዓለማየሁ ፤ ሰኔ 18 ቀን 2011 ዓ/ም

ይህ አጭር ጽሑፍ (1) የሚያተኩረው፤ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን፤ ወለተ ክርስቶስ ተብላ በተሰየመችው፤ የዓለም ስሟ ሲልቪያ ፓንከርስት በሆነው፤ ኢትዮጵያ በፋሺሽቶች በተወረረችበት ጊዜ፤ ከዚያም በሁዋላ ሌሎች ቅኝ ገዢዎች ሊቀራመቷት በቋመጡበት ዘመን በሚያስደንቅ ጀግንነት 20 ዓመት ሙሉ በታገለችው፤ በተከበረች፤ ወይዘሮ የሕይወት ታሪክ ላይ ነው።

ሲልቪያ ፓንከርስት፤ እ.ኤ.አ በ1882 እንግሊዝ ሐገር ተወልዳ፤ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየችው፤ እ.ኤ.አ መስከረም 27 ቀን 1960 አዲስ አበባ ነበር። አስከሬኗ የተቀበረውም፤ ወለተ ክርስቶስ ተሰኝታ፤ እንደ ሌሎች ታላላቅ አርበኞች፤ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ፤ ልዑል አልጋ ወራሽ አስፋ ወሰንና ሌሎች ክቡራን በተገኙበት በቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ነበር። የ50ኛው ዓመት መታሰቢያዋ መስከረም 17 ቀን 2003 ዓ/ም በቅድስት ሥላሴ ቤ/ክ ተከብሯል።

ያላዩት አገር ሲናፍቅ፥ የአዲስ መንግሥት ምኞት (ጌታቸው ኃይሌ)

“መቆየት መልካም ነው፤ የቆየ ሰው የማይሆን ነገር ሲሆን ያያል” ይባላል። ከማይሆኑ ነገሮች አንዱ ያላዩት አገር መናፈቅ ነው። ስለዚህ፥ “ያላዩት አገር አይናፍቅም” ይባላል። መቆየት መልካም ነው፥ እኔም ያላየሁት አገር እስኪናፍቀኝ ቆይቻለሁ። ግን የናፈቀኝ አዲስ ነገር ቢሆንም በኔ አልተጀመረም፤ መንፈሳውያን አባቶቻችንም ናፍቀውታል።

መሪራስ አማን በላይ (፲፱፻፵፪-፳፻፱)

በ1997 ዓ.ም ገደማ ከአማን በላይ መተዋወቅ እንደጀመርን በየጊዜው እየተደዋወልን ለረጅም ሰዓቶች በስልክ እናወራ ነበር። ለሀገሩ ሰው ያለውን ሁሉ ዕውቀት የማካፈል ምኞት ስለነበረው አብዛኛውን ጊዜ የሚናገረው እርሱ ነው። እጅግ ሰፊ ትንታኔና ሐተታ ማቅረብ ይችል ነበር።