Author name: semenaworq

ሳይንስ, ባህል, ታሪክ, Uncategorized

እንሰት – ከቆጮና ቡላ ባሻገር

ይህ ጽሁፍ የእንሰትን ዘርፈብዙ ጠቀሜታና ታሪክ በተለይም መድኃኒትነቱ ላይ  ያተኮረ ይሆናል። እንሰት፤ በሳይንሳዊ ስሙ እንሰት ቬንትሪኮሰም (Enset ventricosum or edule) ከዓለም ሁሉ በኢትዮጵያ ብቻ በምግብነት ጥቅም ላይ የዋለ ዘረ ሙላዱም ከኢትዮጵያ የሆነ የተክል ዓይነት ነው። የአገሪቷ አንድ አምስተኛ (20%) የሚሆነው ሃያ ስድስት ሚሊዮን (26 ሚሊዮን) ሕዝብ የእንሰት ተጠቃሚ እንደሆነ ይገመታል። ተክሉና ዝርያው ከሙዝ ጋር ተመሳሳይ ስለሆነ በእንግሊዝኛ “የውሽት ሙዝ” (false banana) ተብሎ ይታወቃል። እንሰት ከሶስት መቶ በላይ የተለያዩ ዝርያዎች አሉት። ግንዱ፤ ስሩ፤ ቅጠሉ (ኮባው) እና ቃጫው በብዛት ጥቅም ላይ ይውላሉ። እንሰት ከአስር ሺህ ዓመታት በላይ በኢትዮጵያ ሰሜን፥ ደቡብና ምዕራብ የታወቀና ጥቅም ላይ የዋለ እንደሆነ ታሪክ ይናገራል።  በጣና ሐይቅ፣ በሰሜን ተራሮች ዙሪያ እንዲሁም እስከ ሰሜን አዲግራትና በደቡብ ኤርትራ በማእከላዊና ሰሜን ደጋማ አካባቢዎችም ያድግ እንደነበር ታሪክ ያስታውሳል። እንሰት ከሶስት መቶ በላይ የተለያዩ ዝርያዎች አሉት። እንደ ዝርያዎቹ ዓይነት ጠቀሜታዎቻቸውም እንዲሁ ይለያያሉ፤ ለምሳሌም ድርቅንና በሽታን ለመከላከል፤ ለመድኃኒነት፤ ለምግብነት፤ ለቤት መገልገያ፤ ለኢንዱስትሪ ግብአትነት ወዘተ። እንሰት በጉራጌ እሴት/እሰት፥ በሲዳሞ ዊሴ፥ በዳውሮና ወላይታ ኡጦ፥ በጌዴዎ ዎርኪቻ፥ በሃዲያ ስልጤና ከምባታ ዊሳ፥ በትግሬ ጉና ጉና በመባል ይታወቃል። ለብዙ የቤት አገልግሎት የሚውለው ቅጠሉ ኮባ ይባላል።  በምግብነት የሚቀርበው ደግሞ እንደ አካባቢው ቆጮ (ዉሳ፥ ዋሳ፥ ወርቄ…)፥ አሚቾ፥ቡላ ወዘተ እየተባለ ይጠራል።
የእንሰትን ጠቃሚነት እንደሌሎች አዝእርቶች  እውቅና መስጠት፤ የወደፊቱ አንዱ የግብርና ምሰሶ ማድረግ፤ በዋጋ ዝቅተኝነትና አትራፊ የሆኑ ምርቶች ላይ በማትኮር የእንሰት ግብርና እንዳይመነምን የእንሰት አምራቾች እንዲበረታቱ ማድረግ ይገባል።
(ሙሉ ጽሑፉን ለማንበብ ዓርእስቱን ይጫኑ)

ሥነጽሑፍ

መጽሐፈ ምሳሌ ዘጨዋ ተረት፤ እውሩና አንካሳው

ባንድ ከተማ ሽፍታ መጥቶ  ሰው ሁሉ ነፍሱን ለማዳን ሸሸ። ሁለት ሰዎች ቀሩ ይላሉ። እነርሱም እውርና አንካሳ ናቸው። እውሩም የሚመራው ፣ አንካሳውም የሚሸከመው አጥተው ተጨነቁ። ስለዚህ ተማከሩ። እውሩ አንካሳውን ተሸከመው፤ በእውሩ እግር በመፃጉዑ ዓይን እንደ አንድ ሰው ሆነው ሀገር ወዳለበት ደረሱና ነፍሳቸውን ከሞት አዳኑ። ሰው ሁሉ እንዲሁ በምክር ቢተባበር ደኅንነት ይሆንለታል።

ሥነጽሑፍ, ባህል

ስለ ባህል አንዳንድ ነጥቦች – የመነሻ ሀሳብ

ኢትዮጵያ የብዝሀ ብሄረሰቦችና ማህበረሰቦች ሀገር ናት፡፡ እነዚህ የኢትዮጵያ ብሄረሰቦችና ማህበረሰቦች አንደየአካባቢያቸው የተፈጥሮና የአየር ንብረት አንዲሁም በአንድ በኩል በተናጠል በሌላ በኩል ደግሞ እርስ በርስ ባደረጓቸው መስተጋብሮች የፈጠሯቸው ብዝሀ ባህላዊ እሴቶች አሏቸው፡፡ እነዚህ ብዝሀ ባህላዊ እሴቶች ለፈጠሯቸው የህብረተሰብ ክፍሎች እየሰጡት ካሉ ፖለቲካዊ ፣ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጠቀሜታዎች በዘለለ በአገር አቀፍ ደረጃ አንድ የፖለቲካ እንዲሁም ተደጋጋፊ የኢኮኖሚ ማህበረሰብ በመፍጠሩና ጠንካራ ሀገረ መንግስት በመገንባቱ ረገድ የበኩላቸውን የማይታለፍ ድርሻ እንደሚወጡ ይታመናል፡፡ በዚህ የባህል አምድ ስር ስለ ባህል በአጠቃላይ፤ የባህል ምንነት ጠቀሜታና አተገባበር ከኢትዮጵያ አጠቃላይ ብሄረሰቦችና ማህበረሰቦች እንዲሁም አለም አቀፍ ተሞክሮ አንጻር ሃሳቦችን እየሰደርን የምናቀርብ ይሆናል፡፡ ጽሁፉ ተከታታይነት ባለው መልክ የሚቀርብና ሁሎቹንም የባህል ዘውጎችና ዘርፎች የሚዳስስ ሲሆን፤ ለዛሬ የባህልን ትርጓሜ፤ አለም አቀፍና አገር አቀፍ አተያይ በማሳያነት በማቅረብ አሃዱ ብለናል።

ሥነጽሑፍ, ባህል

ሌስላውን ዘረፋ – አጭር የምርምር ማስታወሻ

ይህ አጭር ማስታወሻ የሴማዊ ቋንቋዎች ጥናት አባት ተብለው የሚታወቁት ዎልፍ ሌስላው (Wolf Leslau) በ1961 የዐማርኛ የገደል ማሚቶ ጥምር ቃላት የተሰኘውን መጣጥፋቸውን ለመቃኘትና እውቅና ለመስጠት በአቶ ዳናኤል አበራ ተዘጋጅቶ ቀርቦአል። ሌስላው በጥናቱ ላይ 80 ጥምር ቃላቶችን በመለየት በማሳያነትም እንደ አርቲ ቡርቲ …እንቶ ፈንቶ የሚሉትንና “ምንም ቁም ነገር የለውም… የማይረባ ነው…” ለማለት የሚጠቅሙትን ገልጸዋል። በአሁኑ ጊዜ ከእነዚህ 80 ጥምር ቃላት መካከል 25ቱ ጥቅም ላይ የዋሉ ሲሆኑ 11 ቃላትን አቅራቢው ጨምረዋል ። እነዚህ አስተጋቢ ቃላቶች ከ6 ሚሊዮን የአማርኛ ቃላት ጋር ተጣጥመው ተገኝተዋል።

የሕይወት ታሪክ, ጥናትና ምርምር, ፖለቲካ

የታኅሳስ 1953 ዓ.ም ግርግር በከፊል – ከሻለቃ ያሬድ ቢተው – ዋሺንግተን ዲሲ፣ ሰሜን አሜሪካ – ጥቅምት 2017 ዓ.ም

በጽሁፉ ውስጥ የተካተቱት ቁምነገሮች የመጀመሪያ ደረጃ ምልከታ ምዝገባ ተብለው ከሚጠቀሱት የታሪክ ማጣቀሻ ማስረጃዎች ውስጥ የሚካተቱ ናቸው።
በስነ-ጽሁፍ አቀራረብ ረገድ በወቅቱ የነበረውን የጦማር አጻጻፍ ስልት አጉልቶ በማሳየት በዘመናት መካከል የተፈጠረውን የደብዳቤ እንዲሁም ታሪክ አዘጋገብ የእድገት ወይም ውድቀት ደረጃ አጉልቶ የሚያሳይ በመሆኑ ለስነጽሁፍ ተመራማሪዎች የሚሰጠው ፋይዳ ቀላል አይሆንም።
ከታሪክ አንጻር የወሰድነው እንደሆነ በወቅቱ የተሟላ ማስረጃ ያልተገኘላቸውን እውነታዎች ለህብረተሰባችንና ለታሪክ ተመራማሪዎች በመስጠቱ ረገድ የላቀ አስተዋጻኦ ይኖረዋል:: በዋናነትም የግለታሪክ ዘጋቢው በኩነቱ ወቅት እርምጃው በተወሰደባቸው ቀናት ውስጥ ተሳታፊ የነበሩ በመሆናቸው በአይናቸው የተመለከቱትን የዘገቡ በመሆኑ ከዚህ በፊት ኩነቱን አስመልክቶ የተጻፉ የጥናትና ምርምር ስራዎች ጉድለት በማሟላቱ ረገድ ፋይዳው የጎላ ነው።
የሰምና ወርቅ መጽሔት አዘጋጅዎች

ሳይንስ, ባህል, ታሪክ

የባህል መድኃኒቶች በተለያዩ የዓለም ክፍሎች እና የመድኃኒት ዕፅዋት እንክብካቤ አስፈላጊነት በኢትዮጵያ -(በቅርብ ጊዜ ታትሞ ከወጣው የመጻሕፍት ስብስቦች የተቀዳ) -(ዶ/ር ፈቃዱ ፉላስ)

ኢትዮጵያ በርካታ የብዝሃ ህይወት ሀብቶች አሏት። የባህል መድኃኒት ዕፅዋት ቁጥራቸው እየመነመነ መሄድ፣ በተለይም የመድኃኒት ዕውቀት ያላቸው አረጋውያን ዕልፈተ-ሕይወት አሳሳቢ መሆኑን ኢትዮጵያውያን አጥኚዎች… ጠቁመዋል። ከዚህም ጋር ተያይዞ በልዩ ልዩ ምክንያቶች መላ ማህበረሰቦች ከጊዜ ወደ ጊዜ መፈናቀላቸው፣ የመድኃኒት አዋቂዎች በዕድሜ መግፋትና ወጣቱ ትውልድ ከአረጋውያኑ ለመማር ፈቃደኛ አለመሆኑ ይህን ጠቃሚ ባህል የማቆየቱና የማስተላለፉን ችግር አባብሶታል። የደን መራቆት ትልቅ ችግር አስከትሏል።

ታሪክ, የሕይወት ታሪክ, ጥናትና ምርምር

የሻምበል ሲስተር አስቴር አያና አጭር የሕይወት ታሪክ ከልጃቸው ከያፌት አስራት – ነሐሴ ፲፪, ፳፻፲፭ (August 18, 2023)

የተባበሩት መንግስታት ዋና ጸሐፊ ዳግ ሃመርሾልድ ለግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የላኩት ቴሌግራም:- “ስሟን ገና ያላወቅነው አንዲት ኢትዮጵያዊት ነርስ አንድ አሜሪካዊ መኮንን በአንድ ጂፕ መኪና ውስጥ ተይዞ ሲደበደብ ብቻዋንና ባዶ እጅዋን ልታድነው በሙሉ ልበኝነት ሞክራ ሳይሆንላት ቢቀር ኮንጎዎቹ አሜሪካኑን ይዘዉት ሲሄዱ ሰፈራቸው ድርስ ተከትላ ሔደች፡፡ እዚያም በጥይት ሊገድሏት ቢያስፈራሯትም ተመልሳ ወሬውን ለኢትዮጵያውያኑ ነግራ ሶስቱን አሜሪካውያን አድነዋቸዋል፡፡”  ንጉሡ በመልሳችው ለሲስተር የላኩት መልእክት ” ሥራሽ  ላይ ሆነሽ በፈጸምሸው መልካም ተግባር በጣም ተደስተናል፡፡ ስለ መልካም ሥራሽና ስለ መልካም አደራጎትሽ በጣም እናመሰግንሻለን” ብለው ነበር፡፡ ሲስተርም  በትህትና ሲመልሱ  “ላደርገው የሚገባኝን አገልግሎት በመፈጸሜ የግርማዊነትዎ የምስጋና ቴሌግራም ስለ ደረሰኝ ፤ አነስተኛ አገልጋይዎን በምስጋና ላሰበኝ ግርማዊነትዎ እድሜ በመለመን መሬት እስማለሁ” በማለት ነበር ፡፡

ሀይማኖት, ሥነጽሑፍ, Uncategorized

ስለኢትዮጵያ፡ደራሲያን።

ጽሑፉ፡የፕሮፌሰር፡ታምራት፡አማኑኤል፡ነው። ፕሮፌሰር፡ታምራት፡ከሰማንያ፡ዓመታት፡በፊት፡በትምርትና፡ሥነጥበብ፡ሚኒስቴር፡አማካሪ፡ኾነው ይሠሩ፡ነበር። ነገር፡ግን፡በዚያን፡ጊዜ፡ፕሮፌሰር፡በመባል፡ፈንታ፡ሊቀማእምራን፡ይባሉ፡ነበር። ፕሮፌሰሩ ሲናገሩም :- “ባ፩ኛው፡ዘመን፡በዐማርኛ፡የተጻፈው፡ሥራ፡ እጅግ፡ጥቂት፡ነው።የተጻፈውም፡ላንዳንድ፡ነገሥታት ምስጋና፡ደራሲው፡ካልታወቀ፡የተገጠመ፡ቅኔ፡ነው። ቅኔውም፡በዘመናት፡ውስጥ፡አንድ፡ቋንቋ፡እንደምን፡ ኹኖ፡እየተለዋወጠ፡ለመኼዱ፡ዋና፡ምስክር፡ከመኾኑ በላይ፣በዚያ፡ዘመን፡የነገሥታቱ፡ሥልጣንና፡የተዘረጋበት፡የሰፊው፡አገር፡ኹኔታ፡እንዴት፡እንደነበረ፣ለታ ሪክና፡ለዦግራፊም፡ማስረጃ፡ለመኾን፡ይረዳል። ዐማርኛው፡ዛሬ፡ዘመን፡የማንናገርበትና፡የማንጽፈው፣ለማስተዋሉም፡የሚያስቸግረንና፡የሰዋስው፡አካኼድ፡የተለዋወጠ፡ብዙ፡ቃልና፡አገባብ፡አለበት። እርሱን፡የመሰለ፡ዐማርኛም፡በየዘመኑ፡እየተጻፈ፡ምናልባት፡እስከ፡ ፲፭፻፺፱-፲፮፻፯፡ደርሶ፡ ይኾናል።”

Scroll to Top