ጥናትና ምርምር

የሕይወት ታሪክ, ጥናትና ምርምር, ፖለቲካ

የታኅሳስ 1953 ዓ.ም ግርግር በከፊል – ከሻለቃ ያሬድ ቢተው – ዋሺንግተን ዲሲ፣ ሰሜን አሜሪካ – ጥቅምት 2017 ዓ.ም

በጽሁፉ ውስጥ የተካተቱት ቁምነገሮች የመጀመሪያ ደረጃ ምልከታ ምዝገባ ተብለው ከሚጠቀሱት የታሪክ ማጣቀሻ ማስረጃዎች ውስጥ የሚካተቱ ናቸው።
በስነ-ጽሁፍ አቀራረብ ረገድ በወቅቱ የነበረውን የጦማር አጻጻፍ ስልት አጉልቶ በማሳየት በዘመናት መካከል የተፈጠረውን የደብዳቤ እንዲሁም ታሪክ አዘጋገብ የእድገት ወይም ውድቀት ደረጃ አጉልቶ የሚያሳይ በመሆኑ ለስነጽሁፍ ተመራማሪዎች የሚሰጠው ፋይዳ ቀላል አይሆንም።
ከታሪክ አንጻር የወሰድነው እንደሆነ በወቅቱ የተሟላ ማስረጃ ያልተገኘላቸውን እውነታዎች ለህብረተሰባችንና ለታሪክ ተመራማሪዎች በመስጠቱ ረገድ የላቀ አስተዋጻኦ ይኖረዋል:: በዋናነትም የግለታሪክ ዘጋቢው በኩነቱ ወቅት እርምጃው በተወሰደባቸው ቀናት ውስጥ ተሳታፊ የነበሩ በመሆናቸው በአይናቸው የተመለከቱትን የዘገቡ በመሆኑ ከዚህ በፊት ኩነቱን አስመልክቶ የተጻፉ የጥናትና ምርምር ስራዎች ጉድለት በማሟላቱ ረገድ ፋይዳው የጎላ ነው።
የሰምና ወርቅ መጽሔት አዘጋጅዎች

ታሪክ, የሕይወት ታሪክ, ጥናትና ምርምር

የሻምበል ሲስተር አስቴር አያና አጭር የሕይወት ታሪክ ከልጃቸው ከያፌት አስራት – ነሐሴ ፲፪, ፳፻፲፭ (August 18, 2023)

የተባበሩት መንግስታት ዋና ጸሐፊ ዳግ ሃመርሾልድ ለግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የላኩት ቴሌግራም:- “ስሟን ገና ያላወቅነው አንዲት ኢትዮጵያዊት ነርስ አንድ አሜሪካዊ መኮንን በአንድ ጂፕ መኪና ውስጥ ተይዞ ሲደበደብ ብቻዋንና ባዶ እጅዋን ልታድነው በሙሉ ልበኝነት ሞክራ ሳይሆንላት ቢቀር ኮንጎዎቹ አሜሪካኑን ይዘዉት ሲሄዱ ሰፈራቸው ድርስ ተከትላ ሔደች፡፡ እዚያም በጥይት ሊገድሏት ቢያስፈራሯትም ተመልሳ ወሬውን ለኢትዮጵያውያኑ ነግራ ሶስቱን አሜሪካውያን አድነዋቸዋል፡፡”  ንጉሡ በመልሳችው ለሲስተር የላኩት መልእክት ” ሥራሽ  ላይ ሆነሽ በፈጸምሸው መልካም ተግባር በጣም ተደስተናል፡፡ ስለ መልካም ሥራሽና ስለ መልካም አደራጎትሽ በጣም እናመሰግንሻለን” ብለው ነበር፡፡ ሲስተርም  በትህትና ሲመልሱ  “ላደርገው የሚገባኝን አገልግሎት በመፈጸሜ የግርማዊነትዎ የምስጋና ቴሌግራም ስለ ደረሰኝ ፤ አነስተኛ አገልጋይዎን በምስጋና ላሰበኝ ግርማዊነትዎ እድሜ በመለመን መሬት እስማለሁ” በማለት ነበር ፡፡

ሥነጽሑፍ, የሕይወት ታሪክ, ጥናትና ምርምር

የአቶ ሰይፉ መታፈሪያ የሥነግጥም መድብሎች የጥናት እና የምርምር ሥራዎች ።

ገጣሚ ሲቆጣ (ሰይፉ መታፈሪያ)፣
መጻፍ፣ መጻፍ አለኝ ማቅለም ወረቀት፣ ብእሬን ማስቆጣት ቀይ ደም ማስተፋት።

ዕውቁ ገጣሚ፣ መምህር እና የፎክሎር ባለሙያ ሰይፉ መታፈሪያ ፍሬው በርካታ ያገራችንን እና የአውሮጳን ቋንቋዎች አጥርተው የሚናገሩ እና ጠንቅቀው የሚያውቁ ልሳነ ብዙ ምሁርና ተመራማሪ ናቸው። በኢትዮጵያ እጅግ የተለየ የግጥም አጻጻፍ ስልትን ያስተዋወቁና ያስፋፉ ዕውቅ ገጣሚ ናቸው። እሳቸው እንደሚሉት የግጥማቸው የአጻጻፍ (ዓይነት) „በብዙ ረገድ ባህል-ከተል አይደለም። በዚህ ያጻጻፍ አዲስነት አስገዳጅነትም ስም ስላስፈለገው „ስንኝ አጠፍ ግጥም“ የሚል ስያሜ ሰጥተውታል። ላለፉት ሃምሳ ዓመታት በሀገራችን ቁጥራቸው በርካታ የሆኑ የፎክሎር እና የሥነ ጽሑፍ ተማሪዎችን እና ምሁራንን አፍርተዋል።

ሥነጽሑፍ, ታሪክ, ጥናትና ምርምር

አውሮጳ እና ኢትዮጵያ፤ አመራርና የሥልጣኔ ፖለቲካ

በዘመነ መሳፍንት ስድሳ አምስት ዓመት ሙሉ በማይረባ ምክንያት የተከፋፈለውን፣ የዘቀጠውን፣ የባለገውን ህዝባችንን ከወደቀበት መቀመቅ አውጥተው ኢትዮጵያን ወደጥንት ታላቅነቷ ለመመለስ የኢትዮጵያን ነገሥታት፣ መጀመሪያ አፄ ቴዎድሮስ፣ ቀጥሎ አፄ ዮሐንስ በኋላም አፄ ምኒልክ ያውሮጳን መንግሥታት ድጋፍና ወዳጅነት አጥብቀው ይፈልጉ፣ ይማጠኑ ነበር። አውሮጳውያን ግን የሚፈልጉት የኢትዮጵያን ውድቀቷን፣ ክፍፍሏን፣ ንብረቷንና መሬቷን እንጅ የሕዝቧን ነፃነትና ብልጽግና ስላልነበር በነዚህ ቅን ነገሥታቶች ላይ በየጊዜው ተደጋጋሚ አሳፋሪ ሸርና ተንኮል፣ ሴራና ተራ ማጭበርበር ይፈጽሙባቸው ነበር።

ጥናትና ምርምር

ETHIOPIA: Nile, Renaissance Dam and Political Issues (June 2020) ስለህዳሴ ግድብ እና አባይ ወንዝ እንዲሁም ስለኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብፅ፣ ስለተፈጠረውም የፖለቲካ ቀውስ በሚመለከት ተመዝግበው የተገኙ የዜና ፣የጥናት ጽሑፎችና ሰነዶች ዝርዝር (ሰኔ 2012)፡፡

ይህ መዘርዝር ኢትዮጵያ ልትሰራው ባቀደችው እና በመተግበርም ላይ ባለው የህዳሴ ግድብ ዙሪያ በኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብፅ መካከል የተለያዩ ውይይቶች፣ ስምምነቶችና የሃሳብ ልዩነቶችም ተንፀባርቀዋል:: በመገንባት ላይ ባለው ግድብ የተነሳውን የፖለቲካ ጥያቄ፣ በውሃ ፖለቲካ ዙሪያ የቀርቡ ጥናቶችን ያጠናቀረ ዝርዝር እንዲሆን ጥረት ተደርጓል። የተሟላም ባይሆን በቪዲዮና በመጻሕፍት ሳቢያ የቀረቡ ጥናቶችንና ትችቶችን ጨምረናል። ይህ ጥረት በዚህ የሚገደብ ብቻ ሳይሆን አዳዲስ ውጤቶችን እየጨመረ  የሚቀጥል መዘርዝር እንዲሆን እቅድ አለን።

ጥናትና ምርምር

ስለኢትዮጵያ በዓለም ዙሪያ በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተሰሩ የከፍተኛ ትምሕርት መመረቂያ ጽሑፎች ጥንቅር Dissertations worldwide on Ethiopia in the English Language

ሰምና ወርቅ የጥናትና የምርምር መጽሔት ዝግጀት ክፍል ተቋርጦ የነበረውን ጠቃሚ የጥናት ሰነዶችን እና የምርምር ውጤቶችን ለአንባቢያን የማቅረቢያ ዓምዱን እንደገና ለመቀጠል ወስኗል::
በዚህ ዓምድ ለጊዜው የተገኙትን 170 ያገር ውስጥና የውጭ ሃገር ዩኒቨርሲቲዎች የከፍተኛ ዲግሪ ተመራቂዎች ለምረቃ ያቀረቧቸውን ሃገር-ተኰር የሆኑትን የጥናትና ምርምር ርእሶች ዝርዝር አቅርበናል::

Scroll to Top