ፕሮፌሰር (አብርሃም) አቢይ ፎርድ
ፕሮፌሰር አቢይ ፎርድ በአዲስ አበባ ከተማ በ 1935 ዓ.ፈ. ተወለደ። አባቱና እናቱ ከባርቤዶስ ደሴት ወደ ኢትዮጵያ በመጡበት ጊዜ እናቱ ሚኞን ኢኒስ ፎርድ ባቋቋሙት የልዕልት ዘነበወርቅ ትምህርት ቤት የመማር እድል አግኝቷል። ወደ ዩናይትድ ስቴትስ በመምጣት ባገሩ አየር ኃይል ሰልጥኖ የጦር ጀቶችን ያበር ነበር። ኋላም በኮሎምቢያ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነት ትምህርት ቤት ተመርቋል። ዋሺንግተን ዲ.ሲ በሚገኘው ሃዋርድ ዩኒቨርሲቲ እስከ…