መጽሐፈ ምሳሌ ዘጨዋ ተረት፤ እውሩና አንካሳው
ባንድ ከተማ ሽፍታ መጥቶ ሰው ሁሉ ነፍሱን ለማዳን ሸሸ። ሁለት ሰዎች ቀሩ ይላሉ። እነርሱም እውርና አንካሳ ናቸው። እውሩም የሚመራው ፣ አንካሳውም የሚሸከመው አጥተው ተጨነቁ። ስለዚህ ተማከሩ። እውሩ አንካሳውን ተሸከመው፤ በእውሩ እግር በመፃጉዑ ዓይን እንደ አንድ ሰው ሆነው ሀገር ወዳለበት ደረሱና ነፍሳቸውን ከሞት አዳኑ። ሰው ሁሉ እንዲሁ በምክር ቢተባበር ደኅንነት ይሆንለታል።












