ሳይንስ

ሳይንስ, ባህል, ታሪክ, Uncategorized

እንሰት – ከቆጮና ቡላ ባሻገር

ይህ ጽሁፍ የእንሰትን ዘርፈብዙ ጠቀሜታና ታሪክ በተለይም መድኃኒትነቱ ላይ  ያተኮረ ይሆናል። እንሰት፤ በሳይንሳዊ ስሙ እንሰት ቬንትሪኮሰም (Enset ventricosum or edule) ከዓለም ሁሉ በኢትዮጵያ ብቻ በምግብነት ጥቅም ላይ የዋለ ዘረ ሙላዱም ከኢትዮጵያ የሆነ የተክል ዓይነት ነው። የአገሪቷ አንድ አምስተኛ (20%) የሚሆነው ሃያ ስድስት ሚሊዮን (26 ሚሊዮን) ሕዝብ የእንሰት ተጠቃሚ እንደሆነ ይገመታል። ተክሉና ዝርያው ከሙዝ ጋር ተመሳሳይ ስለሆነ በእንግሊዝኛ “የውሽት ሙዝ” (false banana) ተብሎ ይታወቃል። እንሰት ከሶስት መቶ በላይ የተለያዩ ዝርያዎች አሉት። ግንዱ፤ ስሩ፤ ቅጠሉ (ኮባው) እና ቃጫው በብዛት ጥቅም ላይ ይውላሉ። እንሰት ከአስር ሺህ ዓመታት በላይ በኢትዮጵያ ሰሜን፥ ደቡብና ምዕራብ የታወቀና ጥቅም ላይ የዋለ እንደሆነ ታሪክ ይናገራል።  በጣና ሐይቅ፣ በሰሜን ተራሮች ዙሪያ እንዲሁም እስከ ሰሜን አዲግራትና በደቡብ ኤርትራ በማእከላዊና ሰሜን ደጋማ አካባቢዎችም ያድግ እንደነበር ታሪክ ያስታውሳል። እንሰት ከሶስት መቶ በላይ የተለያዩ ዝርያዎች አሉት። እንደ ዝርያዎቹ ዓይነት ጠቀሜታዎቻቸውም እንዲሁ ይለያያሉ፤ ለምሳሌም ድርቅንና በሽታን ለመከላከል፤ ለመድኃኒነት፤ ለምግብነት፤ ለቤት መገልገያ፤ ለኢንዱስትሪ ግብአትነት ወዘተ። እንሰት በጉራጌ እሴት/እሰት፥ በሲዳሞ ዊሴ፥ በዳውሮና ወላይታ ኡጦ፥ በጌዴዎ ዎርኪቻ፥ በሃዲያ ስልጤና ከምባታ ዊሳ፥ በትግሬ ጉና ጉና በመባል ይታወቃል። ለብዙ የቤት አገልግሎት የሚውለው ቅጠሉ ኮባ ይባላል።  በምግብነት የሚቀርበው ደግሞ እንደ አካባቢው ቆጮ (ዉሳ፥ ዋሳ፥ ወርቄ…)፥ አሚቾ፥ቡላ ወዘተ እየተባለ ይጠራል።
የእንሰትን ጠቃሚነት እንደሌሎች አዝእርቶች  እውቅና መስጠት፤ የወደፊቱ አንዱ የግብርና ምሰሶ ማድረግ፤ በዋጋ ዝቅተኝነትና አትራፊ የሆኑ ምርቶች ላይ በማትኮር የእንሰት ግብርና እንዳይመነምን የእንሰት አምራቾች እንዲበረታቱ ማድረግ ይገባል።
(ሙሉ ጽሑፉን ለማንበብ ዓርእስቱን ይጫኑ)

ሳይንስ, ባህል, ታሪክ

የባህል መድኃኒቶች በተለያዩ የዓለም ክፍሎች እና የመድኃኒት ዕፅዋት እንክብካቤ አስፈላጊነት በኢትዮጵያ -(በቅርብ ጊዜ ታትሞ ከወጣው የመጻሕፍት ስብስቦች የተቀዳ) -(ዶ/ር ፈቃዱ ፉላስ)

ኢትዮጵያ በርካታ የብዝሃ ህይወት ሀብቶች አሏት። የባህል መድኃኒት ዕፅዋት ቁጥራቸው እየመነመነ መሄድ፣ በተለይም የመድኃኒት ዕውቀት ያላቸው አረጋውያን ዕልፈተ-ሕይወት አሳሳቢ መሆኑን ኢትዮጵያውያን አጥኚዎች… ጠቁመዋል። ከዚህም ጋር ተያይዞ በልዩ ልዩ ምክንያቶች መላ ማህበረሰቦች ከጊዜ ወደ ጊዜ መፈናቀላቸው፣ የመድኃኒት አዋቂዎች በዕድሜ መግፋትና ወጣቱ ትውልድ ከአረጋውያኑ ለመማር ፈቃደኛ አለመሆኑ ይህን ጠቃሚ ባህል የማቆየቱና የማስተላለፉን ችግር አባብሶታል። የደን መራቆት ትልቅ ችግር አስከትሏል።

ሳይንስ

ዘረመላዊ ሀብቶች አቅርቦትና ጥቅም ተካፋይነት (ገብርኤል ዳንኤል)

በከፍተኛ ብዝሀ ሕያወት (biological diversity) ፀጋ የታደለች አገር ናት። ብዝሀ ሕይወት በጣም ሰፊና የተወሳሰበ ዓለም አቀፋዊ ቀልብ የሳበ ከፍተኛ የሀብት፥ ምግብ ዋስትናና ንግድ ተፅእኖ ፈጣሪ ጉዳይ ነው። በኢትዮጵያ ከስድስት ሽህ በላይ የአዝርዕት ዝርያ እንዳሉ ይታወቃል። በባለቤትነት ወይም በብሔረ ሙላድነት (origin) የምትታወቅባቸው የብዝሀ ሕይወት ዝርያዎች በርካታ ናቸው። በኢትዮጵያ እነዚህ የተፈጥሮ ሀብቶች በተለያዩ መንገዶች ለሀገር ፍጆታም ሆነ ለውጭ ንግድ ጥቅም ላይ እንደሚውሉ ይታወቃል። በአዃያው የነዚህ የተፈጥሮ ሀብቶች ጥበቃ፥ እንክብካቤና ለንግድ በሚውሉበት ወቅት የማኅበረሰቡ ተሳትፎና ተጠቃሚነት በሚገባው መጠን እንዳልሆነ ይገመታል።

ሳይንስ, ቁጥር 3

“የኢትዮጵያውያን የሳይንስ ሙያተኞች ድርጅት” (ሰይፉ በላይ)

“የዚህ ድርጅት ዋና ዓላማ በሳይንስና ቴክኖሎጂ ጥናትና ምርምር የሚያካሂድና የሚያቀናጅ ስለሚሆን በተለይም ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ የሳይንስ ምሁራን በውጭ ከሚገኘው ኢትዮጵያዊ የሳይንስ ሙያተኛ ጋር ተገናኝተው የጥናትና ምርምር ተለምዶ የሚለዋወጡበትና የሚረዳዱበትን መንገድ የሚፈልጉበት መንኮራኩር መሆን ነው።”

ሳይንስ, ቁጥር 4

“የወባ በሽታን ስለማጥፋት የተደረገ ልማዳዊ ጥናት” (ዮሐንስ)

“ለወባ በሽታ ያገኘሁት የባህል መድኃኒት ከሌሎች የወባ በሽታ መድኃኒቶች ጋር ሲነጻጸር ፍቱን የሆነ ነው። ምክንያቱም ረቂቆች ሕዋሳትን በፍጥነት ለማጥፋት ችሎታ ስላለው እንዲሁም በጭስ ወይም በሲጋራ መልክ ተዘጋጅቶ በአወሳሰድ በቀላል መንገድ መጠቀም ስለሚቻል ነው።”

ሳይንስ, ቁጥር 1

ሳይንስና ቴክኖሎጂ

የአገራችን ሳይንቲስቶች ምንም እንኳን በቁጥራቸው ያነሱ ቢሆኑም በራሳቸው ላይ ጠንካራ እምነት እስካላቸው የሌላ ወገኖቻቸውንም ንቃትና ሕሊና መቀስቀስ እንደሚችሉ እምነት አለን። አውሮጳውያን አፍሪቃ ላይ ካደረሱት በደል አንዱ የራሳችን የሆነውን ባህልና ሕብረተሰብ እንድንንቅና በራሳችን እምነት አጥተን ለእነሱ የአእምሮ ባሪያዎች ሆነን እንድንኖር ማድረጋቸው ሲሆን ይህን አጥብቆ መዋጋቱ የኛ ፋንታ ነው። የራሳችንን ዕድገት በራሳችን እንድንወስን “ሰምና ወርቅ” ይህችን አምድ ከፍቷል።

Scroll to Top