ያላዩት አገር ሲናፍቅ፥ የአዲስ መንግሥት ምኞት (ጌታቸው ኃይሌ)

“መቆየት መልካም ነው፤ የቆየ ሰው የማይሆን ነገር ሲሆን ያያል” ይባላል። ከማይሆኑ ነገሮች አንዱ ያላዩት አገር መናፈቅ ነው። ስለዚህ፥ “ያላዩት አገር አይናፍቅም” ይባላል። መቆየት መልካም ነው፥ እኔም ያላየሁት አገር እስኪናፍቀኝ ቆይቻለሁ። ግን የናፈቀኝ አዲስ ነገር ቢሆንም በኔ አልተጀመረም፤ መንፈሳውያን አባቶቻችንም ናፍቀውታል።