Author name: semenaworq

ሥነጽሑፍ, የሕይወት ታሪክ, ጥናትና ምርምር

የአቶ ሰይፉ መታፈሪያ የሥነግጥም መድብሎች የጥናት እና የምርምር ሥራዎች ።

ገጣሚ ሲቆጣ (ሰይፉ መታፈሪያ)፣
መጻፍ፣ መጻፍ አለኝ ማቅለም ወረቀት፣ ብእሬን ማስቆጣት ቀይ ደም ማስተፋት።

ዕውቁ ገጣሚ፣ መምህር እና የፎክሎር ባለሙያ ሰይፉ መታፈሪያ ፍሬው በርካታ ያገራችንን እና የአውሮጳን ቋንቋዎች አጥርተው የሚናገሩ እና ጠንቅቀው የሚያውቁ ልሳነ ብዙ ምሁርና ተመራማሪ ናቸው። በኢትዮጵያ እጅግ የተለየ የግጥም አጻጻፍ ስልትን ያስተዋወቁና ያስፋፉ ዕውቅ ገጣሚ ናቸው። እሳቸው እንደሚሉት የግጥማቸው የአጻጻፍ (ዓይነት) „በብዙ ረገድ ባህል-ከተል አይደለም። በዚህ ያጻጻፍ አዲስነት አስገዳጅነትም ስም ስላስፈለገው „ስንኝ አጠፍ ግጥም“ የሚል ስያሜ ሰጥተውታል። ላለፉት ሃምሳ ዓመታት በሀገራችን ቁጥራቸው በርካታ የሆኑ የፎክሎር እና የሥነ ጽሑፍ ተማሪዎችን እና ምሁራንን አፍርተዋል።

ሥነጽሑፍ, ታሪክ, ጥናትና ምርምር

አውሮጳ እና ኢትዮጵያ፤ አመራርና የሥልጣኔ ፖለቲካ

በዘመነ መሳፍንት ስድሳ አምስት ዓመት ሙሉ በማይረባ ምክንያት የተከፋፈለውን፣ የዘቀጠውን፣ የባለገውን ህዝባችንን ከወደቀበት መቀመቅ አውጥተው ኢትዮጵያን ወደጥንት ታላቅነቷ ለመመለስ የኢትዮጵያን ነገሥታት፣ መጀመሪያ አፄ ቴዎድሮስ፣ ቀጥሎ አፄ ዮሐንስ በኋላም አፄ ምኒልክ ያውሮጳን መንግሥታት ድጋፍና ወዳጅነት አጥብቀው ይፈልጉ፣ ይማጠኑ ነበር። አውሮጳውያን ግን የሚፈልጉት የኢትዮጵያን ውድቀቷን፣ ክፍፍሏን፣ ንብረቷንና መሬቷን እንጅ የሕዝቧን ነፃነትና ብልጽግና ስላልነበር በነዚህ ቅን ነገሥታቶች ላይ በየጊዜው ተደጋጋሚ አሳፋሪ ሸርና ተንኮል፣ ሴራና ተራ ማጭበርበር ይፈጽሙባቸው ነበር።

ዜና እረፍት, የሕይወት ታሪክ

ተዝካረ ሕይወት – አህመድ ኑር (1949 – 2014 ዓ.ም)

አቶ አህመድ ኑር፤ የሃገሩ ነገር የሚያንገበግበው ፣ የሚቆረቁረው፣ እምነቱንም የሚወድና የሰውን ልጅ ባጠቃላይ የሚያከብርና ጓደኞቹን የሚወድ፤ ባንፃሩ ደግሞ በሰው ዘንድ ተወዳጅ የነበረ ወንድማችን ነበር። በሚጽፋቸው ግጥሞቹ ግጥም የመግጠም ልዩ ችሎታ እንደነበረው ገላጭ ናቸው። በየስብሰባዎች ላይ የሚያነሳቸው ጥያቄዎቹ ሁሉ ጥበብን የተሞሉና ማንንም የማይጎዱ ከአሽሙርና ከአግቦ አገላለጾች ነፃ የሆኑ ቀጥተኛ ነበሩ። ከወሎ ማደጉን እንደትልቅ ነገር የሚያወሳው አቶ አህመድ ኑር የወሎን ዙሪያ ባህልና የንግግር ዘዬ አሳምሮ መግለጽ በመቻሉ የወሎ አምባሳደር የሆነ ያህል ያስቆጥረው ነበር።

ሥነጽሑፍ, ባህል

መጽሐፈ ምሳሌ ዘጨዋ ተረት  

ይህ መጽሐፍ ያልታተመና በዩናይትድ ስቴትስ የኮንግሬስ ቤተመጻሕፍት ውስጥ በአፍሪካና በመካከለኛው ምሥራቅ ዋና ክፍልየኢትዮጵያና የኤርትራ ሃገራት የመጻሕፍት ክምችት ክፍል ውስጥከሌሎች ካልታተሙ የግእዝ፣ የአማርኛና የትግርኛ መጻሕፍት ጋርይገኛል። የተጻፈው በ1911 ዓ.ም ሲሆን ተረቶቹን በጽሑፍያሰፈረው የንጉሥ ወልደጊዮርጊስ አሽከር ነኝ የሚለው ነጋዴው አቶአበሩ የተባለ  የማጂ ከተማ ነዋሪ ሰው ነው። ይህን ያጠናቀረውንየጥንት ተረት መድብል ለወዳጁ  ለእንግሊዝ መንግሥት መኮንንለሜጀር አጥሒል [Major Athil] ሲያበረክት በመጽሐፉ ላይ ተጽፎእንደተገኘው፣ “ ይህን እያዩ እንዲያስታውሱኝ” ከሚል ማሳሰቢያ ጋርነበር። በዚህ መድብል ውስጥ በወረቀት ላይ ተጽፈው የተገኙተረቶች አስራ ሁለት ያህል ናቸው።

ታሪክ

የዳግማዊ አጼ ቴዎድሮስ የሕይወታቸው መጨረሻ ሰዓት እና የመቅደላ ዝርፊያ

ይህ ታሪክ፣ በ1874 [1866 ዓ.ም]  ሄንሪ ኤም. እስታንሊ የተባለው የኒውዮርክ  ሄራልድ ጋዜጣ ተቀጣሪ  እንደ አውሮፖ አቆጣጠር በ1868 በጄኔራል ሮበርት ናፕዬር የተመራው የእንግሊዝ ጦር ጋር ወደ ኢትዮጵያ  በመጓዝ ያከናወነውን “ኮማሲ እና መቅደላ” በተሰኘው የሚመስጥ መጽሐፉ የመዘገበው ነው። ይህ አጭር ጽሑፍም የተጻፈው የንጉሡን ሕይወት ማለፍ ተከትሎ እስታንሊ በገጽ  449-464 ያሰፈረውን ሀተታ ማስረጃ  መሰረት በማድረግ ነው። በተጨማሪም በእውን ያያቸውን ከመቅደላ የተዘረፉትን ቅርሶች ገጽ 454-462 በዝርዝር ያስቀምጣል። የእንግሊዝ ጦር ወደ ኢትዮጵያ የዘመተበት ምክንያት ንጉሡ ለንግሥት ቪክቶሪያ የሁለቱ ሃገራት ወዳጅነት መመስረት እና መጠናከር በተመለከተ ለጻፉላቸው ደብዳቤ መልስ ስለተነፈጋቸው፣ በአጸፋው ያሰሯቸውን የእንግሊዝ መልክተኞች ከእስር ለማስፈታት መሆኑ ሊታወስ ይገባል።

ሥነጽሑፍ

  ‘አኽ፡ሹማዊት ሌሊት፥’                                                         

`አኽ፡ሹም`፥ጥንታዊ፥የ፡`ሳባዊ`፡ሥልጣኔ፡እንደነበራት፡እንጂ፥`ጥንታዊ~ሌሊት`፡እንደ፡አላት፥እስከ፡ዛሬ፡ድረስ፤ፈጽሞ፡ አላውቅም፡ነበር። ብፁዕነታቸው፥ንቡረ~ዕዱ፤የኣጎቴ፡ኣጎት፡ናቸው፥ በብርቱ፥የኅሊና፡ተጽዕኖ፡በሚያሳድር፡ደብዳቤአቸው፥በ፡አጣዳፊ፥ወደ፡`ኣኽ፡ሹም`፡መጥቶ፡እንዲጎበኛቸው፡ስለጠሩት፥ ደብዳቤው፡በደረሰው፡ሠልሥት፥ከ፡ኣሥመራ፡ተነስተን፡የገሠገሥነው።ኣጎቴ፥የ፡ኣሥመራ፡ማዘጋጃ፡ቤት፡ባለ፡ሥልጣን፡ሆኖ፡ከተሾመ፡ቆየ።እኔም፤ለክረምቱ፤የትምህርት፡ቤታችን፡መዘጋት፥ለእረፍት፤ ወደ፡እርሱ፡ዘንድ፡እንድመጣ፡ስለ፡ጠራኝ፤ኣባቴ፤በፍጹም፡ደስታ፤ኣውቶቡስ፡ኣሳፍሮ፡ላከኝ።

የሕይወት ታሪክ

`ዔርታ~ዓሌ`፡~በእንተ፡ነገረ፥`ድንቂቱ`

“`ዔርታ፡ዓሌ፥ወበእንተ፡ነገራ፡ለ`ድንቂቱ`ተረክ ጭብጡ ዕውን ላይ የተመሠረተ ታሪክ ነው” ጃህእርሥዎ፡ሞትባይኖር፡ኪሩብ፡ዔል`፡~ በሚል መጠሪያ ለመጀመሪያ ጊዜ የምናትምለትን ይህን “ዔርታዓሌ ወበእንተ ነገራ ለድንቂቱ” በሚል ርዕስ ባቀረበው ትርክት እንዲታወቅ ቢፈልግም፣ በተለምዶ ስሙ “ጃርሶ ኪሩቤል”ተብሎ የሚታወቀው ይኸው ደራሲና ፀሐፊ በኪነ~ጥበብ ሙያ እና በ( ዔዞቴሪክ~ሳይንስ)ኅቡዕ የነገረ-ሰብ ጥናት እና ምርምር ላይ የተሰማራ ሰው ነው።

ዜና እረፍት

ሊቀ ሊቃውንት ጌታቸው ኀይሌ (1931-2021)

ስለሊቀ ሊቃውንት ጌታቸው ኅይሌ በምናነሳበት ጊዜ በተደጋጋሚ የተገለጠውን ታሪካቸውን ለመድገም ሳይሆን በተለይ ለሰምና ወርቅ ሁለ- ገብ የጥናትና የምርምር መጽሔት ያደረጉትን አስተዋጽዖ ከግል ታሪካቸው እንደ አንድ ምዕራፍ አድርገን ለማስተዋወቅ ከሚል ዓላማ ተነስተን ነው። በቅድሚያ ግን የመጽሔታችን አዘጋጆች ለሊቀ ሊቃውንት ጌታቸው ኅይሌ ያለንን አድናቆት በአንክሮ መግለጥ እንፈልጋለን፤ የመጽሔቱ ባለውለታ ናቸውና።

ሀይማኖት, ታሪክ

የዐፄ ካሌብ ወይም የቅዱስ ኤልስባን* ገድል

ዐፄ  ኢዛና  ሃሌን ንጉሠ ነገሥት 
ዘኢትዮጵያ ተብሎ አስር ዓመት 
ከገዛ በኋላ ከልጆቹ መሃል የአክሱም 
መኳንንት ካሌብን አነገሡ፤ 
ስመ ንግሡም ዳግማዊ 
ዓፄ እለ አጽብሃ ንጉሠ ነገሥት 
ዘኢትዮጵያ መሲሃ እግዚአብሔር 
ተብሎ በ483 ዓም ነገሠ።
ሰላሳ አምስት ዘመን ከገዛ በኋላ 
ሃይማኖቱ ኦሪታዊ የሆነ ዱኖባስ 
ፊንሐስ በናግራን [አሁን የመን 
ተብሎ በሚታወቀው] 
የክርስቲያኖች ቁጥር መብዛቱን 
አይቶ በግዛቱ ውስጥ የነበሩትን 
ከአራት ሺ በላይ ክርስቲያኖችን  
የገደለውን ንጉስ በማስወገዱ 
ይታወቃል። 

የሕይወት ታሪክ

አቶ ዳምጤ አሰማኸኝ (አጭር የህይወት ታሪክ)

ከሁሉ አስቀድሜ የመጽሐፌን ርዕስ “የተዘጋው ምዕራፍ” ብዬ የሰየምኩበትን ምክንያት ልግለጽ። ምክንያቴ ቀላል ነው። ማንኛውም ሰው በራሱ እንጂ በአያትና በቅድመ አያቶች ጥፋት መቅቀጣት እንደሌለበት አምናለሁ። ያ፥ ለኔ የተዘጋ
ምዕራፍ ነውና። ይህን ታሪክ የጻፍኩበት የአባቶቻችንን ስህተት እንዳንደግም፥ ያለሙትን ደግሞ እንድናዳብር እንጂ “አያትህ አያቴን በድሎታልና ብድሩን በአንተ ላይ መመለስ አለብኝ” እየተባባልን እርስ በርሳችን ስንናቆር እንድንኖር አይደለም። ከዓለም ሕዝብ ሁሉ ወደሗላ ያስቀረን ይሄው ተከፍሎ የማያልቅ የበቀል ዕዳ ይመስለኛል። ለዚህ ነው ያ የበቀል ምዕራፍ እንዲዘጋ የፈለግሁት ምጽሐፉንም “የተዘጋው ምዕራፍ” ያልኩት።

Scroll to Top