የአቶ ሰይፉ መታፈሪያ የሥነግጥም መድብሎች የጥናት እና የምርምር ሥራዎች ።

ገጣሚ ሲቆጣ (ሰይፉ መታፈሪያ)፣
መጻፍ፣ መጻፍ አለኝ ማቅለም ወረቀት፣ ብእሬን ማስቆጣት ቀይ ደም ማስተፋት።

ዕውቁ ገጣሚ፣ መምህር እና የፎክሎር ባለሙያ ሰይፉ መታፈሪያ ፍሬው በርካታ ያገራችንን እና የአውሮጳን ቋንቋዎች አጥርተው የሚናገሩ እና ጠንቅቀው የሚያውቁ ልሳነ ብዙ ምሁርና ተመራማሪ ናቸው። በኢትዮጵያ እጅግ የተለየ የግጥም አጻጻፍ ስልትን ያስተዋወቁና ያስፋፉ ዕውቅ ገጣሚ ናቸው። እሳቸው እንደሚሉት የግጥማቸው የአጻጻፍ (ዓይነት) „በብዙ ረገድ ባህል-ከተል አይደለም። በዚህ ያጻጻፍ አዲስነት አስገዳጅነትም ስም ስላስፈለገው „ስንኝ አጠፍ ግጥም“ የሚል ስያሜ ሰጥተውታል። ላለፉት ሃምሳ ዓመታት በሀገራችን ቁጥራቸው በርካታ የሆኑ የፎክሎር እና የሥነ ጽሑፍ ተማሪዎችን እና ምሁራንን አፍርተዋል።

ተዝካረ ሕይወት – አህመድ ኑር (1949 – 2014 ዓ.ም)

አቶ አህመድ ኑር፤ የሃገሩ ነገር የሚያንገበግበው ፣ የሚቆረቁረው፣ እምነቱንም የሚወድና የሰውን ልጅ ባጠቃላይ የሚያከብርና ጓደኞቹን የሚወድ፤ ባንፃሩ ደግሞ በሰው ዘንድ ተወዳጅ የነበረ ወንድማችን ነበር። በሚጽፋቸው ግጥሞቹ ግጥም የመግጠም ልዩ ችሎታ እንደነበረው ገላጭ ናቸው። በየስብሰባዎች ላይ የሚያነሳቸው ጥያቄዎቹ ሁሉ ጥበብን የተሞሉና ማንንም የማይጎዱ ከአሽሙርና ከአግቦ አገላለጾች ነፃ የሆኑ ቀጥተኛ ነበሩ። ከወሎ ማደጉን እንደትልቅ ነገር የሚያወሳው አቶ አህመድ ኑር የወሎን ዙሪያ ባህልና የንግግር ዘዬ አሳምሮ መግለጽ በመቻሉ የወሎ አምባሳደር የሆነ ያህል ያስቆጥረው ነበር።

`ዔርታ~ዓሌ`፡~በእንተ፡ነገረ፥`ድንቂቱ`

“`ዔርታ፡ዓሌ፥ወበእንተ፡ነገራ፡ለ`ድንቂቱ`ተረክ ጭብጡ ዕውን ላይ የተመሠረተ ታሪክ ነው” ጃህእርሥዎ፡ሞትባይኖር፡ኪሩብ፡ዔል`፡~ በሚል መጠሪያ ለመጀመሪያ ጊዜ የምናትምለትን ይህን “ዔርታዓሌ ወበእንተ ነገራ ለድንቂቱ” በሚል ርዕስ ባቀረበው ትርክት እንዲታወቅ ቢፈልግም፣ በተለምዶ ስሙ “ጃርሶ ኪሩቤል”ተብሎ የሚታወቀው ይኸው ደራሲና ፀሐፊ በኪነ~ጥበብ ሙያ እና በ( ዔዞቴሪክ~ሳይንስ)ኅቡዕ የነገረ-ሰብ ጥናት እና ምርምር ላይ የተሰማራ ሰው ነው።

አቶ ዳምጤ አሰማኸኝ (አጭር የህይወት ታሪክ)

ከሁሉ አስቀድሜ የመጽሐፌን ርዕስ “የተዘጋው ምዕራፍ” ብዬ የሰየምኩበትን ምክንያት ልግለጽ። ምክንያቴ ቀላል ነው። ማንኛውም ሰው በራሱ እንጂ በአያትና በቅድመ አያቶች ጥፋት መቅቀጣት እንደሌለበት አምናለሁ። ያ፥ ለኔ የተዘጋ
ምዕራፍ ነውና። ይህን ታሪክ የጻፍኩበት የአባቶቻችንን ስህተት እንዳንደግም፥ ያለሙትን ደግሞ እንድናዳብር እንጂ “አያትህ አያቴን በድሎታልና ብድሩን በአንተ ላይ መመለስ አለብኝ” እየተባባልን እርስ በርሳችን ስንናቆር እንድንኖር አይደለም። ከዓለም ሕዝብ ሁሉ ወደሗላ ያስቀረን ይሄው ተከፍሎ የማያልቅ የበቀል ዕዳ ይመስለኛል። ለዚህ ነው ያ የበቀል ምዕራፍ እንዲዘጋ የፈለግሁት ምጽሐፉንም “የተዘጋው ምዕራፍ” ያልኩት።

ፕሮፌሰር ሰይፉ በላይ (1951 – 2019)

ፕሮፌሰር ሰይፉ በላይና እኔ የተዋወቅነው እኔ የሐዋርድ ዩኒቨርሲቲ ተማሪና  የቤተ መጻሕፍቱ ሠራተኛ እያለሁ ነበር። እርሱ በዚያ ጊዜ የሳይንስ ፋክልቲ ተማሪ ነበር። ከተዋወቅን በጥቂት ጊዜ ውስጥ ቀደም ሲል  አውቀው ከነበረው አቶ ሙሉጌታ ከበደ  ጋር  ተቀናጅተን  አንድ  መጽሔት  እንድናቋቁም  ባቀረብኩላቸው ሃሳብ ላይ በመስማማታቸው በውይይት ሰምና ወርቅ ሁለገብ የጥናትና የምርምር መጽሔት በሚል ርእስ መጽሔት የማቋቋሙንና  በተግባር የመግለጹን እርምጃ   ተያያዝነው። እኔ የመጽሔቱ ዋና አዘጋጅ እንድሆን፣  ፕሮፌሰር ሰይፉና አቶ ሙሉጌታ ደግሞ የአዘጋጅው ቦርድ አባላት በመሆን አብረውኝ ሊሰሩ ተስማማን። የመጀመሪያውን እትም በምናዘጋጅበት ጊዜ እንደስምምነታችን በሁሉም የእውቀት ዘርፍ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያን ያሉበትን ደረጃ በመገምገም እንድንጀምር የሚል ሃሳብ ስለነበረ ፕሮፌሰር ሰይፉ በሳይንስና ቴክኖሎጂ ያለውን ድርሻ በሚገባ ሰርቶ አቅርቦልናል። ከዚህም የመንደርደሪያ ጥራዝ በኋላ ፕሮፌሰር ሰይፉ በላይ በቀጣዩ ጥራዝ ላይ ማለትም ጥር 1979 ዓ.ም በታተመው እትም ላይ “የፕላስቲክ ኪነ ጥበብ” በሚል ርእስ ላይ ሰርቷል፤  ሰኔ 1979 ዓ.ም በታተመው ላይ ደግሞ “ጥንታዊ የብረት ቴክኖሎጂ በኢትዮጵያ” በሚል ርእስ አንድ መልካም ጽሑፍ ለአንባቢያን አቅርቧል። በመጨረሻም “የኢትዮጵያውያን የሳይንስ ሙያተኞች ድርጅት” በሚል አንድ ተጨማሪ ጽሑፍ ጥር 1981 ዓ.ም በወጣው እትም ላይ አቅርቧል። ፕሮፌሰር ሰይፉ በላይ ከሐዋርድ ዩኒቨርሲቲ በባዮቴክኖሎጂ ከፍተኛ ድግሪ ከተቀበለ በኋላ፥   በአሜሪካ መንግስት መሥሪያ ቤቶች (በዋልተር ሪድስና ኤን አይ ኤች – Walter…

ፕሮፌሰር (አብርሃም) አቢይ ፎርድ

ፕሮፌሰር አቢይ ፎርድ በአዲስ አበባ ከተማ በ 1935 ዓ.ፈ. ተወለደ። አባቱና እናቱ ከባርቤዶስ ደሴት ወደ ኢትዮጵያ በመጡበት ጊዜ እናቱ ሚኞን ኢኒስ ፎርድ ባቋቋሙት የልዕልት ዘነበወርቅ ትምህርት ቤት የመማር እድል አግኝቷል። ወደ ዩናይትድ ስቴትስ በመምጣት ባገሩ አየር ኃይል ሰልጥኖ የጦር ጀቶችን ያበር ነበር። ኋላም በኮሎምቢያ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነት ትምህርት ቤት ተመርቋል። ዋሺንግተን ዲ.ሲ በሚገኘው ሃዋርድ ዩኒቨርሲቲ እስከ…

መሪራስ አማን በላይ (፲፱፻፵፪-፳፻፱)

በ1997 ዓ.ም ገደማ ከአማን በላይ መተዋወቅ እንደጀመርን በየጊዜው እየተደዋወልን ለረጅም ሰዓቶች በስልክ እናወራ ነበር። ለሀገሩ ሰው ያለውን ሁሉ ዕውቀት የማካፈል ምኞት ስለነበረው አብዛኛውን ጊዜ የሚናገረው እርሱ ነው። እጅግ ሰፊ ትንታኔና ሐተታ ማቅረብ ይችል ነበር።

“ብላታ መርስዔ ኀዘን ወ/ቂርቆስ” (አምኃ መርስዔ ኀዘን)

ብላታ መርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ መጋቢት 17 ቀን 1891 ዓ.ም. ሸዋ ጅሩ ውስጥ እምቧጮ መግደላዊት በተባለ ስፍራ ተወለዱ። አባታቸው አለቃ ወልደ ቂርቆስ አልታመን ይባላሉ። እሳቸውም በደብረ ሊባኖስና በእንጦጦ ማርያም የቤተ ልሔምን መዝገበ ድጓ ሲያስተምሩ የነበሩና በዜማ መምህርነት የታወቁ ናቸው። እናታቸው ወይዘሮ የሸዋ ወርቅ ምናጣ ይባላሉ። የአባታቸው አጎት አለቃ ገብረ ክርስቶስ የብሉይና የሐዲስ ሊቅና የቅኔ መምህር የነበሩ በንጉሥ ኃይለ መለኮት፣ በአጼ ዮሐንስና በአጼ ምኒልክ ቤተ መንግሥት እጅግ የተከበሩ ሰው ነበሩ።

“ዘመንፈስ ቅዱስ አብርሃ” (ገ/ኢ ጐርፉ)

አቶ ዘመንፈስ ቅዱስ አብርሃ ከአባታቸው ከነጋድራስ አብርሃ ወልዱ እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ወለላ ተክሉ በዓድዋ ከተማ እንደ ኢትዮጵያውያን አቆጣጠር በ1905 ዓ.ም. ተወለዱ። አባታቸው ነጋድራስ አብርሃ በከተማው ከነበሩት ታዋቂ ነጋዴዎች መካከል አንዱ ነበሩ። ልጃቸው የቤተ ክህነትን ትምህርት በዘመኑ ገናና ወደ ነበረው የዓድዋ ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን አስገብተው ከፊደል መቁጠር ዳዊትና ወንጌል ንባብ ቀጥሎም ለዲቁና የሚያበቃውን የቃልና የዜማ ትምህርት እንዲማሩ አደረጉ። ይሁንና ገና የዐሥራ ሦስት ዓመት ወጣት እያሉ አባታቸው በድንገተኛ የወባ ሕመም ስለሞቱ ትምህርታቸውን አቋርጠው…