ቁጥር 10, የሕይወት ታሪክ

“ዘመንፈስ ቅዱስ አብርሃ” (ገ/ኢ ጐርፉ)

አቶ ዘመንፈስ ቅዱስ አብርሃ ከአባታቸው ከነጋድራስ አብርሃ ወልዱ እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ወለላ ተክሉ በዓድዋ ከተማ እንደ ኢትዮጵያውያን አቆጣጠር በ1905 ዓ.ም. ተወለዱ። አባታቸው ነጋድራስ አብርሃ በከተማው ከነበሩት ታዋቂ ነጋዴዎች መካከል አንዱ ነበሩ። ልጃቸው የቤተ ክህነትን ትምህርት በዘመኑ ገናና ወደ ነበረው የዓድዋ ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን አስገብተው ከፊደል መቁጠር ዳዊትና ወንጌል ንባብ ቀጥሎም ለዲቁና የሚያበቃውን የቃልና የዜማ ትምህርት እንዲማሩ አደረጉ። ይሁንና ገና የዐሥራ ሦስት ዓመት ወጣት እያሉ አባታቸው በድንገተኛ የወባ ሕመም ስለሞቱ ትምህርታቸውን አቋርጠው…

ቁጥር 10, ባህል

ባህልና ሕዝብ (ይርጋ መንግሥቱ እስጢፋኖስ)

የዛሬይቱ ኢትዮጵያ ከ81 (ሰማንያ አንድ) በላይ የሆኑ የብሔር፣ የብሔረሰብና የማህረሰብ ቅንብር ያላት መሆኑ ግልጽ ነው። በመቶዎች የሚቆጠሩ አባላት ብቻ ከአላቸው ባህላቸውና የዝርያቸው ሐረግ ሊዋጥና – ጨርሶም ሊጠፋ ጥቂት ከቀራቸው ማህበረሰቦች አንስቶ፣ ብዙ ሚሊዮን አባላት እስከ አሏቸው አያልና ሠፋፊ መሬት እስከ ያዙት የኦሮሞና የአማራ ብሔሮች ባህሏን የሚያበለጽጉና ሕብረሰባዊነቷን የሚያጠናክሩ፣ ሕብሯን የሚያሞሽሩ ህዝቦች የሚኖሩባት አገር ነች።

ቁጥር 8- 9 ልዩ እትም, ፖለቲካ

“ዘመናዊ እና ታሪካዊ ብሔርተኝነት” (ተስፋዬ ደመላሽ)

“ለኢትዮጵያ ውስብስብ የአገር አስተዳደር ችግሮች ዘመናዊ የፖለቲካ ጽንሰ ሐሳቦች ፈርጆች መመልከቻ ወይም መፍቻ የሚሆኑት እንዴት ነው? ዘመናዊ ጽንሰ ሐሳቦች ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምንነትና አንድነት ምን ትርጉምስ ሊኖራቸው ይችላል?”

Scroll to Top