“ዘመንፈስ ቅዱስ አብርሃ” (ገ/ኢ ጐርፉ)
አቶ ዘመንፈስ ቅዱስ አብርሃ ከአባታቸው ከነጋድራስ አብርሃ ወልዱ እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ወለላ ተክሉ በዓድዋ ከተማ እንደ ኢትዮጵያውያን አቆጣጠር በ1905 ዓ.ም. ተወለዱ። አባታቸው ነጋድራስ አብርሃ በከተማው ከነበሩት ታዋቂ ነጋዴዎች መካከል አንዱ ነበሩ። ልጃቸው የቤተ ክህነትን ትምህርት በዘመኑ ገናና ወደ ነበረው የዓድዋ ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን አስገብተው ከፊደል መቁጠር ዳዊትና ወንጌል ንባብ ቀጥሎም ለዲቁና የሚያበቃውን የቃልና የዜማ ትምህርት እንዲማሩ አደረጉ። ይሁንና ገና የዐሥራ ሦስት ዓመት ወጣት እያሉ አባታቸው በድንገተኛ የወባ ሕመም ስለሞቱ ትምህርታቸውን አቋርጠው…








