ሳይንስ

ዘረመላዊ ሀብቶች አቅርቦትና ጥቅም ተካፋይነት (ገብርኤል ዳንኤል)

በከፍተኛ ብዝሀ ሕያወት (biological diversity) ፀጋ የታደለች አገር ናት። ብዝሀ ሕይወት በጣም ሰፊና የተወሳሰበ ዓለም አቀፋዊ ቀልብ የሳበ ከፍተኛ የሀብት፥ ምግብ ዋስትናና ንግድ ተፅእኖ ፈጣሪ ጉዳይ ነው። በኢትዮጵያ ከስድስት ሽህ በላይ የአዝርዕት ዝርያ እንዳሉ ይታወቃል። በባለቤትነት ወይም በብሔረ ሙላድነት (origin) የምትታወቅባቸው የብዝሀ ሕይወት ዝርያዎች በርካታ ናቸው። በኢትዮጵያ እነዚህ የተፈጥሮ ሀብቶች በተለያዩ መንገዶች ለሀገር ፍጆታም ሆነ ለውጭ ንግድ ጥቅም ላይ እንደሚውሉ ይታወቃል። በአዃያው የነዚህ የተፈጥሮ ሀብቶች ጥበቃ፥ እንክብካቤና ለንግድ በሚውሉበት ወቅት የማኅበረሰቡ ተሳትፎና ተጠቃሚነት በሚገባው መጠን እንዳልሆነ ይገመታል።

ባህል, ታሪክ, ፖለቲካ

ያላዩት አገር ሲናፍቅ፥ የአዲስ መንግሥት ምኞት (ጌታቸው ኃይሌ)

“መቆየት መልካም ነው፤ የቆየ ሰው የማይሆን ነገር ሲሆን ያያል” ይባላል። ከማይሆኑ ነገሮች አንዱ ያላዩት አገር መናፈቅ ነው። ስለዚህ፥ “ያላዩት አገር አይናፍቅም” ይባላል። መቆየት መልካም ነው፥ እኔም ያላየሁት አገር እስኪናፍቀኝ ቆይቻለሁ። ግን የናፈቀኝ አዲስ ነገር ቢሆንም በኔ አልተጀመረም፤ መንፈሳውያን አባቶቻችንም ናፍቀውታል።

ሥነጽሑፍ, ባህል

“የአንድ ኢትዮጵያዊ ደራሲ ሕመም” (እንዳለጌታ ከበደ)

በዚህ ዘመን ያለ አንድ ኢትዮጵያዊ ደራሲ በአብዛኛው ራሱ ጽፎ፣ ራሱ አርሞ፣ ራሱ አስተይቦ፣ ራሱ ፊደል ለቅሞ፣ ራሱ ማተሚያ ቤት ፈልጎ፣ ራሱ አሰራጭቶ፣ ራሱ ማስተዋወቂያ ሠርቶ፣ ራሱ አስመርቆ፣ ራሱ ለኅትመት ያወጣውን ገንዘብ ሰብስቦ፣ … ይኖራል። ብዙ ነው ድካሙ።

ሥነጽሑፍ, ታሪክ, የሕይወት ታሪክ

መሪራስ አማን በላይ (፲፱፻፵፪-፳፻፱)

በ1997 ዓ.ም ገደማ ከአማን በላይ መተዋወቅ እንደጀመርን በየጊዜው እየተደዋወልን ለረጅም ሰዓቶች በስልክ እናወራ ነበር። ለሀገሩ ሰው ያለውን ሁሉ ዕውቀት የማካፈል ምኞት ስለነበረው አብዛኛውን ጊዜ የሚናገረው እርሱ ነው። እጅግ ሰፊ ትንታኔና ሐተታ ማቅረብ ይችል ነበር።

ቁጥር 10, የሕይወት ታሪክ

“ብላታ መርስዔ ኀዘን ወ/ቂርቆስ” (አምኃ መርስዔ ኀዘን)

ብላታ መርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ መጋቢት 17 ቀን 1891 ዓ.ም. ሸዋ ጅሩ ውስጥ እምቧጮ መግደላዊት በተባለ ስፍራ ተወለዱ። አባታቸው አለቃ ወልደ ቂርቆስ አልታመን ይባላሉ። እሳቸውም በደብረ ሊባኖስና በእንጦጦ ማርያም የቤተ ልሔምን መዝገበ ድጓ ሲያስተምሩ የነበሩና በዜማ መምህርነት የታወቁ ናቸው። እናታቸው ወይዘሮ የሸዋ ወርቅ ምናጣ ይባላሉ። የአባታቸው አጎት አለቃ ገብረ ክርስቶስ የብሉይና የሐዲስ ሊቅና የቅኔ መምህር የነበሩ በንጉሥ ኃይለ መለኮት፣ በአጼ ዮሐንስና በአጼ ምኒልክ ቤተ መንግሥት እጅግ የተከበሩ ሰው ነበሩ።

ቁጥር 10, ባህል, ታሪክ

“የግማደ መስቀል ወደ ኢትዮጵያ መምጣት” (ጌታቸው ኃይሌ)

የግማደ መስቀል መገኘት በብዙ ታሪክ ተመዝግቧል። ይህ ጽሑፍ እንደሚያሳየው፥ ከእኛ ዘንድ የተገኘው ታሪክ በሁለት ነገር ይለያል። አንደኛ፦ መስቀሉን አፈላልጋ ስላገኘችው ስለ ንግሥት እሌኒ ታሪክ የሚነገረው ከሌላ ዘንድ የሌለ ሰፋ ያለና ሲያነቡት የሚጥም ነው። ሁለተኛ፦ ስለግማደ መስቀሉ ወደ ኢትዮጵያ መምጣት ብዙ የታሪክ ሰነዶች መስክረዋል።

ቁጥር 10, ፍልስፍና

“የዘርአ ያዕቆብ (ወርቄ) እና የሬኔ ዴካርት ፍልስፍና” (ፈንታሁን ጥሩነህ)

ዘርአ ያዕቆብ ከአክሱም የመነጨ ፈላስፋ ነው። ዴካርት ደግሞ ከፈረንሳይ ሀገር ይመነጫል። ሁለቱም ፈላስፋዎች በአንድ ዘመን ኖረዋል። በትውልድ ዓመትም ብዙ አይራራቁም። … ሬኔ ዴካርት የሚታወቀው የመጀመሪያ ፈረንሳዊ ብሎም አውሮጳዊ ፈላስፋ በመሆኑ ነው። በሌላ በኩል ደግሞ ዘርአ ያዕቆብ እስካሁን ያለውን መጠነኛ ታዋቂነት ያገኘው ዘመንፈስ ቅዱስ አብርሃ ከግዕዝ ወደአማርኛ ተርጉመው ባሳተሙት ፤ ሐተታ ዘዘርአ ያዕቆብ አክሱማዊ ወወልደ ሕይወት እንፍራዛዊ በተሰኘው መጽሐፍ ሳቢያ ነው።

ቁጥር 10

ርዕሰ አንቀጽ

መሠረተ: ሐሳብ፤

ሰምና ወርቅ መጽሔትን መልሶ ማቋቋም ለምን አስፈለገ?

ሰምና ወርቅ መጽሔት በአማርኛ ቋንቋ እየታተመ የሚወጣ የምርምርና የጥናት መጽሔት ሆኖ በ1979 ዓ.ም. መታተም ጀመረ። በዚያን ወቅት ከኢትዮጵያ እየፈለሰ የሚወጣው ኢትዮጵያዊ እጅግ ብዙ ነበር። ነገር ግን እርስ በራስ ለመገናኘት፥ ሐሳብ ለሐሳብ ለመገበያየት የሚያስችል መድረክ ባለመኖሩ የስደቱ ኑሮ ለብዙኅኑ አሰልችና ተደጋጋሚ የሆነ ፈሊጥ ወደ መሆን ደርሶ ነበር። በዚህ መካከል አንዳንድ ምሁራን የአማርኛ ፊደልን በኮምፒውተር የመጠቀም ችሎታን ስለፈጠሩና እያሳደጉ በመምጣታቸው ለህብረተሰቡ አንድ አገናኝ የሆነ መጽሔት የማቋቋሙ አስፈላጊነት እጅግ ጎልቶ ይታይ ነበር።…

Scroll to Top