ዘረ ያዕቆብና ገብረ ህይወት ባይከዳኝ፤ ሁለት የዘመናዊነት እሳቤዎች በኢትዮጵያ ፍልስፍና፤ በፋሲል መርአዊ፤ (ሌክቸረር ፤ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ፍልስፍና ት/ክፍል)

በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ የዘመናዊነት ሀሳብ ከአንድ ትውልድ ወደ ሌላ ትዉልድ፣ ከአንድ ዘመን ወደ ሌላው ዘመን እየተሸጋገረ ይሄዳል፡፡ ስለዚህም እያንዳንዱ ማህበረሰብ የበለጠ ዘመናዊና በለውጥ የሚያምን መሆኑን ለማሳየት ይሞክራል፡፡ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የዘመናዊነት ሀሳብ መገለጫዎች በተፈጥሮ የተለያዩ ናቸው፡፡ ስለዚህም በስነጥበብ፣ በፍልስፍና፣ በማህበረሰብ ትችና ዘመናዊ ትምህርት ውስጥ የተለያዩ ሀሳቦች ተንፀባርቀው እናገኛለን፡፡

በፍልስፍና መስክ ኢትዮጵያዊው ፈላስፋ ዘረያዕቆብ፣ የባህልና የወግ አስተሳሰቦችን ትችት በማዳበር በማህበረሰቡ ውስጥ ምክንያታዊነትና ማህበረሰባዊ ፍትህ እንዲሰፍን “ሐተታ” የተሰኘ ስራውን ለማዳበር ሞክሯል፤ ከዚህ ጋር በተያያዘ ኢትዮጵያዊው ምሁር ነጋድራስ ገብረህይወት ባይከዳኝ የሀገር በቀል ጥበብንና ምዕራባዊ ስልጣኔን ያጣመረ የዕድገት ጐዳና ለመቀየስ ሲሞክር ነበር፡፡ በነዚህ ሙከራዎች ላይ ተመርኩዘን ዘመናዊነት የበለጠ በኢትዮጵያ ውስጥ እንዲዳብር ምክንያታዊ የሆነ ማህበረሰብ እንድያብብ ማድረግ  ያስፈልጋል፡፡

“የዘርአ ያዕቆብ (ወርቄ) እና የሬኔ ዴካርት ፍልስፍና” (ፈንታሁን ጥሩነህ)

ዘርአ ያዕቆብ ከአክሱም የመነጨ ፈላስፋ ነው። ዴካርት ደግሞ ከፈረንሳይ ሀገር ይመነጫል። ሁለቱም ፈላስፋዎች በአንድ ዘመን ኖረዋል። በትውልድ ዓመትም ብዙ አይራራቁም። … ሬኔ ዴካርት የሚታወቀው የመጀመሪያ ፈረንሳዊ ብሎም አውሮጳዊ ፈላስፋ በመሆኑ ነው። በሌላ በኩል ደግሞ ዘርአ ያዕቆብ እስካሁን ያለውን መጠነኛ ታዋቂነት ያገኘው ዘመንፈስ ቅዱስ አብርሃ ከግዕዝ ወደአማርኛ ተርጉመው ባሳተሙት ፤ ሐተታ ዘዘርአ ያዕቆብ አክሱማዊ ወወልደ ሕይወት እንፍራዛዊ በተሰኘው መጽሐፍ ሳቢያ ነው።

ፍልስፍናና ፈጠራ

ኢትዮጵያውያን የራሳቸው ፍልስፍና ሆነ የመፈላሰፊያና የፈጠራ ዘዴና ዘይቤ የላቸውም የሚል አስተሳሰብ ለብዙ ጊዜ ሲነገር የቆየ ነው። ብዙዎቻችን ይህንን አስተሳሰብ ያለምርምር አምነንበት ኖረናል። ይህ በኢትዮጵያውያን ላይ የተሰነዘረው አመለካከት ምንጩ የት እንደሆነ ማወቅ ባያዳግትም በተጨባጭ ለማሳየት የሚረዳንን የጀርመኑን ፈላስፋ የሔግልን ጽሑፍ እንጠቅሳለን። ሔግል ስለአፍሪቃውያን በጅምላ የሰጠው አስተያየት እንዲህ ይላል፤