“ረኀብና ተስቦ በኢትዮጵያ” (ጌታቸው ኃይሌ)
“ረኃብና ተስቦ በኢትዮጵያ በታሪክ በኩል የቱን ያህል እንደነበሩ ለማሳየት አንዳንድ ማስታወሻዎችን ከታሪክ ገጾች ልጥቀስ።”
“ረኃብና ተስቦ በኢትዮጵያ በታሪክ በኩል የቱን ያህል እንደነበሩ ለማሳየት አንዳንድ ማስታወሻዎችን ከታሪክ ገጾች ልጥቀስ።”
“ይህ ጽሑፍ ከሞላ ጐደል ረሃብና ድርቅ ሰው ሰራሽ ችግር ነው፤ ስለዚህም መፍትሔው ሰው ሰራሽ ነው ወደሚለው ያዘማል።”
“የምዕራቡ ጋዜጣ አዘጋጅዎችና ሪፖርተሮች ከአባቶቻቸው ኮሎኒያሊስቶች የተረከቡትን ኢትዮጵያን የማጥላላት ዘመቻ ዛሬ ኢትዮጵያ በደረሰባት አሳዛኝ ማኅበራዊ ቀውስ ሳቢያ በማስታከክ ነባር ቂማቸውንና አዲስ ርዕዮተ ዓለማዊ ጥላቻቸውን ለመወጣት በጽሑፎቻቸው ይቃጣቸዋል።”
“ከዚህ ቀጥሎ የታተመው ራሳቸው ያረቀቁት የሕይወት ታሪካቸው የተገኘው ከቤተሰቦቻቸው ሲሆን የሕይወት አመራራቸውን በቅርብ ሆነው የተከታተሉ ቤተሰቦቻቸው የጻፉት መግቢያ ጽሑፍ አብሮ ቀርቧል።”
“ኢትዮጵያ የሚለው ቃል ምን ማለት ነው? ከወዴትስ የመጣ ቃል ነው? የሚሰጡት መልሶች ግን አጥጋቢ አይደሉም። እንዲያውም አልፎ አልፎ ጥራዝ ነጠቅና የተዛባ የተሳሳተም መልስ ሲሰጥ እንሰማለን።”
“በዚህ ዓምድ በሰፊው ሊታወቁ የሚገባቸው የመሰሉንን አንዳንድ ጥንታዊ ታሪክ የያዙ ሰነዶችን ለማቅረብ እንሞክራለን።”
“ያ ለካፊ ሙስሊኒ ሳይቸግረው ለከፈውና ነው እንጅ አፈ ቄሣር ባይሆንማ ኖሮ ለአፈ ወርቅ ሥነጽሑፍ ምን ሰሀ ይወጣለት ነበር?”
“ፍትሐ ነገሥትና በወቅቱ የነበረው የፍርድ አሰጣጥ የዘመኑ ማኅበረሰብ ሥርዐት ነጸብራቅ እንደመሆኑ መጠን የሰጠው ግልጋሎትም ማኅበረሰቡን በየደረጃው ከፋፍሎ ነው።”
የምንነሳው ኢትዮጵያ በታሪኳ ጥንታዊነት መታወቋን ምርኩዝ በማድረግ ነው። ይህ ሲባል ግን ጥንታዊ ታሪኳ በጅምላ የሚያኮራ ነበር ከሚል ትምክት ለመነሳት አይደለም። ከዚህ ጥንታዊነት ጋር ተያይዞ ሲወርድ ሲዋረድ የመጣውን ባህልና ያሁኑ ትውልድ የወረሰውን ማንኛውንም ታሪክ መመልከት ይኖርብናል። የጥንትና የቅርቡ ታሪክ በሚነሳበት ጊዜ የምንማረው ምንድነው ከሚል ጥያቄ አንፃር መሆን ይኖርበታል። መጥፎውን መጥፎ፣ ጥሩውን ጥሩ ለማለት ግን ታሪክን የምናይበትና የምንመረምርበት መመልከቻ ዘዴ የግዴታ እንዲኖረን ሊያስፈልግ ነው።