“የኢትዮጵያ ረሀብና የምዕራብ ጋዜጦች” (እነ ቆሪቾ ፈይሣ)

“የምዕራቡ ጋዜጣ አዘጋጅዎችና ሪፖርተሮች ከአባቶቻቸው ኮሎኒያሊስቶች የተረከቡትን ኢትዮጵያን የማጥላላት ዘመቻ ዛሬ ኢትዮጵያ በደረሰባት አሳዛኝ ማኅበራዊ ቀውስ ሳቢያ በማስታከክ ነባር ቂማቸውንና አዲስ ርዕዮተ ዓለማዊ ጥላቻቸውን ለመወጣት በጽሑፎቻቸው ይቃጣቸዋል።”

“ኢትዮጵያ” የሚለው ቃል

“ኢትዮጵያ የሚለው ቃል ምን ማለት ነው? ከወዴትስ የመጣ ቃል ነው? የሚሰጡት መልሶች ግን አጥጋቢ አይደሉም። እንዲያውም አልፎ አልፎ ጥራዝ ነጠቅና የተዛባ የተሳሳተም መልስ ሲሰጥ እንሰማለን።”

ታሪክ በኢትዮጵያ

የምንነሳው ኢትዮጵያ በታሪኳ ጥንታዊነት መታወቋን ምርኩዝ በማድረግ ነው። ይህ ሲባል ግን ጥንታዊ ታሪኳ በጅምላ የሚያኮራ ነበር ከሚል ትምክት ለመነሳት አይደለም። ከዚህ ጥንታዊነት ጋር ተያይዞ ሲወርድ ሲዋረድ የመጣውን ባህልና ያሁኑ ትውልድ የወረሰውን ማንኛውንም ታሪክ መመልከት ይኖርብናል። የጥንትና የቅርቡ ታሪክ በሚነሳበት ጊዜ የምንማረው ምንድነው ከሚል ጥያቄ አንፃር መሆን ይኖርበታል። መጥፎውን መጥፎ፣ ጥሩውን ጥሩ ለማለት ግን ታሪክን የምናይበትና የምንመረምርበት መመልከቻ ዘዴ የግዴታ እንዲኖረን ሊያስፈልግ ነው።