መጽሐፈ ምሳሌ ዘጨዋ ተረት ።
ይህ መጽሐፍ ያልታተመና በዩናይትድ ስቴትስ የኮንግሬስ ቤተመጻሕፍት ውስጥ በአፍሪካና በመካከለኛው ምሥራቅ ዋና ክፍልየኢትዮጵያና የኤርትራ ሃገራት የመጻሕፍት ክምችት ክፍል ውስጥከሌሎች ካልታተሙ የግእዝ፣ የአማርኛና የትግርኛ መጻሕፍት ጋርይገኛል። የተጻፈው በ1911 ዓ.ም ሲሆን ተረቶቹን በጽሑፍያሰፈረው የንጉሥ ወልደጊዮርጊስ አሽከር ነኝ የሚለው ነጋዴው አቶአበሩ የተባለ የማጂ ከተማ ነዋሪ ሰው ነው። ይህን ያጠናቀረውንየጥንት ተረት መድብል ለወዳጁ ለእንግሊዝ መንግሥት መኮንንለሜጀር አጥሒል [Major Athil] ሲያበረክት በመጽሐፉ ላይ ተጽፎእንደተገኘው፣ “ ይህን እያዩ እንዲያስታውሱኝ” ከሚል ማሳሰቢያ ጋርነበር። በዚህ መድብል ውስጥ በወረቀት ላይ ተጽፈው የተገኙተረቶች አስራ ሁለት ያህል ናቸው።