የመጠጥ ቤት ቅኔ
“ትሰሙኝ እንደሆነ ልንገራችሁ በውነት፣
በራሰው አንጀት ነው ቅቤውን መጣጣት።”
“ትሰሙኝ እንደሆነ ልንገራችሁ በውነት፣
በራሰው አንጀት ነው ቅቤውን መጣጣት።”
“ፊደሎች ጥንት እንደተፈጠሩ በነባርነት ሊኖሩ አይችሉም። ወረታቸው ያልፍና ለዛቸውን ያጣሉ። በዚያን ጊዜ አንዳንድ ታታሪዎች ወይም ደርጅቶች እየተነሱ ክብደታቸውንና አስቸጋሪነታቸውን እየገመገሙ አጣጣላቸውም ሆነ ቅርፃቸው ለጽሕፈት እንዲያመችና ለትምህርት እንዲቀል ማሻሻያ አሳቦችን ያበረክቱላቸዋል።”
“ያ ለካፊ ሙስሊኒ ሳይቸግረው ለከፈውና ነው እንጅ አፈ ቄሣር ባይሆንማ ኖሮ ለአፈ ወርቅ ሥነጽሑፍ ምን ሰሀ ይወጣለት ነበር?”
“ይህ ጽሑፍ መሠረታዊ ብለን ከምንመድባቸው ጽሑፎች ይመደባል። በተለምዶ የሚሠራባቸውን ቃላት ከትክክለኛው መሠረታቸው (መነሻቸው) ጋር አያይዞ ትክክለኛውን ፍችና ጥቅም እንዲሰጡ ሙከራ ያደርጋል። በተለይም የግዕዝ ቋንቋ ያለውን ጥቅም ለማወቅ ይረዳል ብለን እንገምታለን።”
“ይህ ጽሑፍ የቅኔ ቤት ወይም የቅኔ ትምህርት ቤት ተብሎ የሚታወቀውን ጥንታዊ ተቋም ይመለከታል። ጥናቱም ቅኔና የሥነጽሑፍ ተግባሩን፣ ቅኔና የንድፈ ሀሳብ አወቃቀሩን፣ እና ቅኔና የፍልስፍና ተግባሩን ይዳስሳል።”
በኢትዮጵያ ከየብሔረሰቡ የሚፈልቁ ብዙ አሸብራቂና አስደሳች ትርጉም የሚሰጡ የባሕል ቅርሶች አሉ ። ብዙ ዓይነት ጣዕመ ዜማ ያላቸው የሙዚቃ መሳሪያዎችም ቁጥራቸው በርካታ ነው። ብሔራት የባህላቸውን ምንነት የሚገልጹባቸው የራሳቸው የሆነ የስእልና የቅርጻ ቅርጽ አቀራረጽ አሳሳልና ልዩ ልዩ ብልሃት ሞልቷል። ይህ ሁሉ አስደናቂ ነገር አብይ ቅርስ ስለሆነ ይህ ትውልድ የራሱ የሆነውን ቅርሳዊ ሃብት ኮርቶበት ለመጪው ትውልድ በቂ መሰረት ለማቆየት አካባቢውን አጥንቶና መርምሮ ማወቅና ማሳወቅ ማቆየት ይገባዋል።